1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ኢራቅ የተወረረችበት 10ኛ ዓመት

ሰኞ፣ መጋቢት 9 2005

«---አዲሲቱ ኢራቅን እንድትገነቡ እንረዳችኋለን።በነፃይቱ ኢራቅ በጎረቤቶቻችሁ ላይ የሚፈፀም ወረራ አይኖርም።ተቃዋሚዎች አይገደሉም።የማሰቃያ ጉሮኖዎች፥ የመድፈሪያ ክፍሎች አይኖሩም።የአምባገነኑ ዘመን እያበቃ ነዉ።የነፃነታችሁ ቀን

https://p.dw.com/p/17znW
Black smoke from a car bomb attack is seen in Baghdad, Iraq, Thursday, March, 14, 2013. A string of explosions tore through central Baghdad within minutes of each other on Thursday, followed by what appeared to be a coordinated assault by gunmen who battled security forces in the Iraqi capital, according to officials. Authorities say more than a dozen have been killed. (AP Photo/Karim Kadim)
የባግዳድ ዉሎ-የቦምብ ፍንዳታምስል picture alliance/AP Photo

ተቃርቧል።» ቡሽ

መጋቢት 18 2003 (ዘመኑ በሙሉ እንደ ጎርጎሮሳዉያኑ አቆጣጠር ነዉ) የባግዳድ አደባባዮች።

ዋሽንግተን፥-ፕሬዝዳት ጆርጅ ደብሊዉ ቡሽ።«ሳዳም ሁሴንን እና ወንድ ልጆቹ በሃያ-አራት ሠዓታት ዉስጥ ኢራቅን ለቀዉ መዉጣት አለባቸዉ።»ዛሬ አስረኛ ዓመቱ።በሳልስቱ ባግዳድ ትነድ፥ ኢራቅ ትጋይ፥ ትወድም ገባች።የወረራዉ አስረኛ ዓመት መነሻ፥ የኢራቅ የዛሬ እዉነት ማጣቃሻ፥ የወረራዉ ዉጤት የአስተምሕሮት መድረሻችን ነዉ።ላፍታ አብራችሁኝ ቆዩ።

«ዛሬ ብዙ ኢራቃዉያን የንግግሬን ትርጉም በራዲዮ ይሰሙኛል።ለነሱ መልዕክት አለኝ።ወታደራዊ ዘመቻዉን ከጀመርን (ጥቃቱ) የሚያነጣጥረዉ ሐገራችሁን በሚገዛዉ ሕገ-ወጥ ግለሰብ ላይ ነዉ።በናንተ ላይ አይደለም።ተጣማሪ ሐይላችን ሥልጣን ሲይዝ የምትፈልጉትን ምግብና መድሐኒት እናቀርብላችኃለን።»

መጀመሪያ ግን ያዉ ቦምብ ሚሳዬል መላክ አለበት።መጋቢት አስራ-ዘጠኝ ለሃያ-አጥቢያ።ተላከ። ባግዳድ።

የአሜሪካዉ አልበቃም።የብሪታንያም ታከለበት።የያኔዉ የብሪታንያ ጠቅላይ ሚንስትር ቶኒ ብሌር።

«ዛሬ ማታ የብሪታንያ ሴትና ወንድ ወታደሮች የአየር፥ የምድርና የባሕር ዉጊያ ጀምረዋል። ተልዕኳቸዉ ሳዳም ሁሴንን ከስልጣን ማስወገድና ኢራቅን የአዉዳሚ የጦር መሳሪያ ትጥቅ ማስፈታት ነዉ።»

አዉዳሚ ጦር መሳሪያ-አደገኛ ነዉ።ቶኒ ብሌር ያኔ ብለዉት እንደነበረዉ ደግሞ አደጋዉ በጣም አስጊ ነዉ።ሳዳም ሁሴን በአርባ-አምስት ደቂቃ ዉስጥ ሊተኩስት ተዘጋጅተዋል።በአርባ-አምስት ደቂቃ።

«ኢራቅ ኬሚካዊና ባዮሎጂካዊ ጦር መሳሪያ እንዳላት መረጃዉ ያረጋግጣል።ሳዳም እነዚሕን መሳሪያዎች ማምረት መቀጠላቸዉን፥ መሳሪያዎቹን ለመተኮስ ወታደራዊ እቅድ እንዳላቸዉ እና እቅዱ በአርባ አምስት ደቂቃ ዉስጥ ገቢር እንደሚሆን (መረጃዉ) ያጠቃልላል።»

አርባ አምስት ደቂቃ።ሌሎችም ሰጉ፥ ፈሩ።እና ጦር አዘመቱ፥ በጥቅሉ ከመቶ ሰባ ሺሕ በላይ የዉጪ ጦር።ደካማይቱን፥ግን የነዳጅ ዘይት ሐብታሚቲን ኢራቅን ሌት ተቀን ከምድር፥ ካየር፥ ከባሕር ይወቅጣት ያዘ።

«ለኢራቆች የሽብር መዋቅሩን እንበጣጥሰላችኋለን።አዲሲቱ ኢራቅን እንድትገነቡ እንረዳችኋለን።በነፃይቱ ኢራቅ በጎረቤቶቻችሁ ላይ የሚፈፀም ወረራ አይኖርም።ተቃዋሚዎች አይገደሉም።የማሰቃያ ጉሮኖዎች፥ የመድፈሪያ ክፍሎች አይኖሩም።የአምባገነኑ ዘመን እያበቃ ነዉ።የነፃነታችሁ ቀን ተቃርቧል።»

ሳዳም አስወግዶ፥ በአርባ አምስት ደቂቃ የሚተኮሰዉን የኢራቅን የአዉዳሚ ጦር መሳሪያ ማርኮ፥ ለኢራቆች ሠላም፥ ዲሞክራሲ፥ ነፃነት፥ ብልፅግና ለማስፈን የዘመተዉ ጦር፥ በተከታታይ ጦርነት የላሸቀዉን፥ አስራ-ሁለት ዓመት በፀና ማዕቀብ የደቀቀዉን የኢራቅ ጠላቱን ለመፈረካከስ ሰወስት ሳምንት አልፈጀበትም።

ሚያዚያ ዘጠኝ አሜሪካ መራሹ ጦር ባግዳድን ተቆጣጠረ።የሳዳም ሁሴይን ሐዉልትም፥ የአሜሪካኖችን ባንዲራ ለብሶ፥ ባሜሪካኖች ታንክ ተጎትቶ፥ አሜሪካኖችን ባሰለፉት ሕዝብ ጭብጨባ፥ ፉጨት ታጅቦ ተገነደሰ።

በቡሽ ቋንቋ የሽብር መዋቅሩ ይበጣጠስ ያዘ።የአምባገነኑ ሥርዓት አበቃ።ኢራቆችም ነፃ ወጡ። ከእንግዲሕ አዲሲቱ ኢራቅ ነች።የመካከለኛዉ ምሥራቅ የሰላም፥ ዲሞክራሲ፥ የብልፅግና የፍትሕ አብነት የምትሆነዋ አዲሲቱ ኢራቅ-አሉ አሳቸዉ።ምን ገዷቸዉ።

«አምባገነኑ ሲወገድ እነሱ (ኢራቆች) ለመካከለኛዉ ምሥራቅ የሥላምና የሉዓላዊነት ምሳሌ የምትሆን ነፃ ሐገር መመስረት ይችላሉ።ዩናይትድ ስቴትስና ሌሎች ሐገራትም በዚያ አካባቢ ሠላምና ነፃነትን ለማሥረፅ አበክረዉ ይሠራሉ።»

የሳዳም ሁሴይን ሁለት ወንድ ልጆች ለአካለ መጠን ካልደረሰ የልጅ ልጃቸዉ ጋር ጭዳ ከሆኑ ዘጠኝ ዓመት አልፎታል።እንደ ጀግና ጦር ሜዳ ሊወድቁ ሲፎክሩ ኖረዉ እንደ አይጥ ከጉርጓድ የተመዘዙት ሳዳም ሁሴይን ራሳቸዉ ባደባባይ ከተንጠለጠሉ ስድስት ዓመት አለፈ።

የጥንታዊ ሥልጣኔ መገኛይቱ፥ የነዳጅ ሐብታሚቱ፥ የመካከለኛዉ ምሥራቅ የዘመናይ ትምሕርት የእዉቀት ምሳሌይቱ ኢራቅም ለመካከለኛዉ ምሥራቅ አይደለም ለመላዉ ዓለም ምሳሌ ሆናለች።የሠላም ግን አይደለም፥ የሽብር እንጂ።የብልፅግናም አይደለም፥ የእልቂት ፍጅት፥ የጥፋት ዉድመት፥ የሥቃይ-እንግልት፥ የሥደት ምሳሌ እንጂ።

ከወራራዉ ጀምሮ ዕለት በዕለት በሚያሽብራት ቦምብ ሚሳዬል አርባ ሺሕ ያሕል ታጣቂዎች፥ አንድ መቶ አርባ ሺሕ ሰላማዊ ሰዎች አልቀዉባታል።አራት ሚሊዮን ያክል አድም ተሰዶ፥ አለያም ተፈናቅሎ ምፅዋት ለማኝ ነዉ።አካሉ የጎደለ፥ ያበደ፥ የቆሰለዉን፥ ቤቱ ይቁጠረዉ። ከአቡ ግራይብ ወይሕኒ ቤት እስከ ፋሉጃ መንደሮች በአሜሪካኖችና በተባባሪዎቻቸዉ ጦር ግፍ የተዋለበት፥ የተደፈረ፥ የተገረፈዉን የቆጠረዉ ካለ ዘመድ-ወዳጁ ብቻ ነዉ።

የሐያሊቱ ሐገር ሐያል ጦር ጠቅላይ አዛዥ ጆርጅ ደብሊዉ ቡሽ ዛሬ ከዚያ ትልቅ ሥልጣናቸዉ ላይ የሉም።በአርባ አምስት ደቂቃ ዉስጥ ይተኮሳል የተባለዉ የኢራቅ ጅምላ ጨራሽ ፥አዉዳሚ ጦር መሳሪያም ያኔም አልነበረም።ኋላም አልተገኘም።«አለ» ብለዉ የዋሹት፥ «ሳዳም ሁሴን ሊተኩሱት ነዉ» እያሉ ዓለምን ያስፈራሩት ሐይላት ኋላ ሐቁ ሲፈጋ መዋሸታቸዉን ማመን ግድ ነበራባቸዉ የ።

«ሳዳም ባዮሎጂያዊና ኬሚካዊ ጦር መሳሪያ አላቸዉ፥ እያመረቱም ነዉ የሚለዉ መረጃ ሐሰት ነዉ።ይሕን አምናለሁ።ተቀብያለሁም።»

ጠቅላይ ሚንስትር ቶኒ ብሌር።እና እንደ ብልሕ ወጣት ፖለቲከኛ ተደንቀዉ፥ ተወደዉ፥ የያዙትን ሥልጣን በኢራቅ ሰበብ እንደ ዉሸታም መሪ ተወቅሰዉ፥ ተተችተዉ ሥልጣናቸዉን በግድ መልቀቅ፥ መርማሪ ኮሚቴ ፊት ጥፋታቸዉን መናዘዝ ነበረባቸዉ።የፍትሕ ነፃነት፥ የዲሞክራ አብነቱ ዓለም ግን አንዳቸዉንም በፍርድ ቤት ተጠያቂ ግን አላደረገም።

ወረራዉ፥ ዉሸቱ፥ ዉሸቱን ማመኑ አንዱም ለኢራቅ አልፈየደም።ለአሜሪካ፥ ለብሪታንያ፥ ተከታዮቻቸዉም አልጠቀመም።አሜሪካና ተባባሪዎችዋ አራት ሺሕ ስምንት መቶ አምስት ወታደሮቻቸዉ ተገድለዉባቸዋል።አራት ሺሕ አምስት መቶ ያሕሉ አሜሪካዉያን ናቸዉ።ከሐምሳ አንድ ሺሕ በላይ ቆስሏል።ከአንድ ሺሕ አምስት መቶ በላይ የኮንትራት ሠራተኞች ተገድለዋል።አርባ አራት ሺሕ ቆስለዋል።

አሜሪካና ተባባሪዎችዋ ወደ አንድ ትሪሊዮን ዶለር የሚቆጠር ገንዘብ ከስክሰዋል።ከብራዚል እስከ ፊሊፒንስ ያሉ ሐገራት የዜጎቻቸዉን፥ ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት እስከ ዓለም ቀይ መስቀል ማሕበሩ ያሉ ድርጅቶች የእዉቅ ባለሥልጣን፥ የተራ ሠራተኞቻቸዉን ሕይወት መገበር ግድ ነበረባቸዉ። ወረራዉ ለዓለም ሠላምም የተከረዉ የለም።ምዕራቡ ዓለም በምጣኔ ሐብት ድቀት፥ በገንዘብ ኪሳራ፥ግራ ቀኝ የሚላጋዉም፥ የተቀረዉም ዓለም በኪራ የሚዳክረዉ ከወረራዉ በሕዋላ ነዉ።

የቀድሞዋ የዩናይትድ ስቴት ዉጪ ጉዳይ ሚንስትር ወይዘሮ ሒላሪ ክሊንተን ሥልጣናቸዉን ሊለቁ ዕለታት ሲቀራቸዉ ባራት ዓመት ዘመነ-ሥልጣናቸዉ የሠሩት ነገር «የተበላሸዉን የአሜሪካ በጎ ሥም ዝና ወደነበረበት ለመመለስ መጣር» ነበር አሉ።

የፖለቲካ አዋቂ ዳንኤል ሐሚልተን እንደሚሉት የኦባማ መስተዳር በጥቅሉ፥ የክሊንተን በተናጥል ያደረጉት ጥረት በከፊልም ቢሆን ተሳክቷል።

«እንደሚመስለኝ ሒላሪ ክሊንተን ከፕሬዝዳት ኦባማ ጋር ሆነዉ፥ በቡሽ ዘመን የጠፋዉን አሜሪካ በዓለም የነበራትን መልካም ገፅታ ለማሻሻል ሞክረዋል።በአንዳዶች አይን ፕሬዝዳት ኦባማ መጥፎዉን ገፅታ አሻሽለዉታል።የክሊንተንም አስተዋፅኦ ቀላል አይደለም።»

ፕሬዝዳት ጆርጅ ደብሊዉ ቡሽና ጠቅላይ ሚንስትር ቶኒ ብሌር ኢራቅን የወረሩት፥ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅትን ደንብና ሕግ ጥሰዉ፥ የወዳጆቻቸዉን ምክር አጣጥለዉ፥ የመረጣቸዉን ሕዝብ ሳይቀር የአብዛኛዉን ዓለም ሕዝብ ተቃዉሞና ተማፅኖ ደፍልቀዉ ነዉ።እብሪት ማን አሕሎኝነታቸዉ ከሳዳም ሁሴን ሕይወት፥ ሥልጣን እኩል የሚሊዮን ኢራቃዉያንን፥ የብዙ ሺሕ አሜሪካዉያንን በመቶ የብዙ መቶ ብሪታንያዉያንን ሕይወት፥ አካል፥ ሐብት በማጥፋት አልቆመም።ዩናይትድ ስቴትስ ከሁለተኛዉ የዓለም ጦርነት ወዲሕ የነበራትን ተወዳጅነት፥ ክብር፥ ሥም ዝናም አጉድፎታል።የዓለም ሠላምንም አናግቶታል።አስር ዓመቱ።ከእንግዲሕስ? ነጋሽ መሐመድ ነኝ ቸር ያሰማን።

Former British Prime Minister Tony Blair leaves the High Court in London Monday, May 28, 2012 after he gave evidence to the Leveson media inquiry. Blair testified Monday that he never challenged the influential British press because doing so would have plunged his administration in a drawn-out and politically damaging fight. The Leveson inquiry is Britain's media ethics probe that was set up in the wake of the scandal over phone hacking at Rupert Murdoch's News of the World, which was shut in July 2011,after it became clear that the tabloid had systematically broken the law. (Foto:Lefteris Pitarakis/AP/dapd).
ቶኒ ብሌየርምስል dapd
Saddam Hussein 1980
ሳዳም ሁሴይንምስል AP
US President George W. Bush addresses the nation from the Oval office of the White House late 19 March 2003 in Washington, DC, announcing he had launched war against Iraq, promising a "broad and concerted campaign" to disarm Baghdad and topple Saddam Hussein. Foto: Luke FRAZZA dpa
ጆርጅ ደብሊዉ ቡሽምስል picture-alliance/dpa
FILE - An image of an Iraqi prisoner in Abu Ghraib prison in Bhagdad allegedly standing on a box with his head covered by a hood and electrical wires attached to his hands. The photo was first seen on the CBS television program Sixty Minutes II aired 28 April 2004. Several US soldiers have been reprimanded and President George W. Bush stated 05 May 2004 in an Arabic language television interview, 'that what took place in that prison does not represent the America that I know'. The Afghan Taliban on Thursday, January 12, 2012 condemned as «inhuman» a video allegedly showing US soldiers urinating on the bodies of what appeared to be Afghan insurgents. He charged that US soldiers had committed similar «crimes» since the 2001 US-led invasion of Afghanistan and said they would «only shorten Americans' and their allies' lives here in Afghanistan.» (Zu dpa Hintergrund "Soldaten schockierten mehrfach mit Filmen und Fotos") EPA/DSK EDITORIAL USE ONLY +++(c) dpa - Bildfunk+++
አቡግራይብ ወሕኒ ቤትምስል picture-alliance/dpa
An Iraqi Kurdish woman visits the grave of her relative, Omar Mustafa who was killed in a gas attack by former Iraqi president Saddam Hussein in 1988 at the memorial site of the victims in the Kurdish town of Halabja, 300 kms (190 miles) northeast of Baghdad on March 16, 2012. Some 5,000 civilians, mostly women and children, were killed in the chemical gas attack by Saddam Hussein's airforce as part of a campaign to crush a Kurdish rebellion. AFP PHOTO/SAFIN HAMED (Photo credit should read SAFIN HAMED/AFP/Getty Images)
የወረራዉ ገሚስ ዉጤትምስል Safin Hamed/AFP/Getty Images

ነጋሽ መሐመድ

ተክሌ የኋላ











ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ