1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ኢትዮጵያና የዓለም ንግድ ድርጅት

ረቡዕ፣ መስከረም 3 2004

ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት ዓባል ለመሆን ከሚጥሩት አዳጊ አገሮች መካከል አንዷ እንደሆነች ይታወቃል። ማመልከቻ ከገባችም ይሄው ሰባት ዓመታት ያህል አልፈዋል።

https://p.dw.com/p/RlNU
ምስል AP

እርግጥ መንግሥት ዓባልነቱን ለዕድገት እንደሚበጅ አድርጎ ቢመለከተውም በሌላ በኩል አገሪቱን የምዕራባውያን ሽቀጥ ማራገፊያ ከማድረግ ያለፈ ጠቀሜታ አይኖረውም ሲሉ የሚቃወሙት ተቺዎችም አልጠፉም። ይህ ጥርጣሬና ስጋት ወደፊትም መነሣት መቀጠሉ የሚቀር አይመስልም። ለመሆኑ በአጠቃላይ ኢትዮጵያ እስካሁን ለዓለም ንግድ ድርጅት ዓባልነት ቅድመ-ግዴታ የሆኑትን ማለዘቢያ ደምቦች በማስፈኑ ረገድ ያደረገችው ዕርምጃ ምን ያህል ነው? በድርድሩ እስካሁን ምን የተገኘ ዕርምጃስ አለ? በነዚህ ጥያቄዎች ላይ በስኮትላንድ-ዳንዲ ዩኒቨርሲቲ የዓለምአቀፍ ንግድ ምሁር የሆኑትን ዶር/መላኩ ደስታን አናግረናል።

መሥፍን መኮንን

ሒሩት መለሠ