ኢትዮጵያዊው ምርጥ የዩኒቨርስቲ ምሁር
ረቡዕ፣ ታኅሣሥ 2 2006ማስታወቂያ
ዶክተር ሙላቱ ለማ በአሜሪካ ጆርጅያው የሳቫና ስቴት ዩኒቨርስቲ በሂሳብ የትምህርት ክፍል በተማሪዎቻቸው ከፍተኛ ከበሬታና ፍቅር ያገኙ መምህር ናቸው ። በርካታ የሂሳብ ጥናትና ምርምር ሥራዎችን አቅርበዋል ።በራሳቸው ስም የሚጠራ የሂሳብ ስሌት እሳቤም ፈጥረዋል ። እኚህ መምህር ከመላው አሜሪካን ለውድድር ከቀረቡ 360 ከፍተኛ መምህራን እጎአ የ2013 ምርጥ የዩኒቨርስቲ ምሁር በመባል ተመርጠዋል ። የዋሽንግተን ዲሲው ዘጋቢኢችን አበበ ፈለቀ ኢትዮጵያዊውን የሂሳብ መምህርና ተመራማሪ ዶ/ር ሙላቱ ለማን አነጋግሮ ተከታዩን ዘገባ ልኮልናል ።
አበበ ፈለቀ
ኂሩት መለሰ
ነጋሽ መሐመድ