1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ኢጋድና የታሰበው የሽብርተኝነት መቋቋሚያ ማዕከል

ረቡዕ፣ የካቲት 20 2005

የምሥራቅ አፍሪቃ በይነ መንግሥታት የልማት ባለሥልጣን፤ ሽብርተኝነትን መቋቋም የሚቻልበት ማዕከል ለማቋቋም አቅድ ያለው መሆኑን የኢጋድ የሰላምና ፀጥታ ክፍል ዋና ኀላፊ ፤ ኮማንደር አበበ ሙሉነህ አስታውቁ። እስከ መጪው ዓመት ታኅሳስ ወር ማለቂያ ሊቋቋም

https://p.dw.com/p/17mt2

ይችላል የተባለው ማዕከል፤ በአዲስ አበባ እንደሚሆን ቢታሰብም፤ በትክክል የት ሊሆን እንደሚችል፤ የሚወሰነው በቀጣይ ዐቢይ ስብሰባ እንደሚሆን ፤ ኮማንደር አበበ አያይዘው ገልጸዋል።

የምሥራቅ አፍሪቃ በይነ-መንግሥታት፣ የልማት ባለሥልጣን፣ በመጀመሪያ ረሃብንና ድርቅን ለመቋቋም፣ ብሎም ልማትን ለማስፋፋት መቋቋሙ የሚታወስ ነው። ይኸው የመንግሥታት ትብብር፣ የተለያዩ ቅርንጫፍ አካላት ያሉት ሲሆን፤ ከአነዚህ መካከል አንዱ፣ የፀጥታና የሰላም ክፍል ነው። የምሥራቅ አፍሪቃም ሆነ የአፍሪቃው ቀንድ አካባቢ መንግሥታትተጋፈጡት የተባለው ዋናው የሽብር ተግባር የቱ ነው? ኮማንደር አበበ ሙሉነህ----

የምሥራቅ አፍሪቃ በይነ-መንግሥታት የልማት ባለሥልጣን አባል ሃገራት፣ ዘርፈ-ብዙ ችግሮች አሉባቸው። አንዱ የተጠቀሰው ሽብርተኝነትን መልሶ መቋቋም የሚለው ዐቢይ ግምት ያገኘበት ምክንያት ምን ይሆን?! የ ኢ ጋ ድ የሰላምና ፀጥታ ክፍል ዋና ኃላፊ ኮማንደር አበበ ሙሉነህ---

ተክሌ የኋላ

አርያም ተክሌ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ