ኦባማ ለአፍሪቃውያን
ረቡዕ፣ ጥር 13 2001ማስታወቂያ
ትናንት ምሽት የዩኤስ አሜሪካ ፕሬዚዳንት ሆነው ቃለ መሃላ ከፈፀሙት ባራክ ኦባማ፤ አፍሪቃ በአያሌው እንደምትጠብቅ ታዋቂ የሆኑ ፖለቲከኞችና ግለሰቦች እየገለፁ ነው። የቀድሞው የአፍሪቃ አንድንነት ዋና ፀሀፊ ሳሌም አህመድ ሳሌምና ኬንያዊቷ የሠላም ኖቤል ተሽላሚ ዋንጋሪ ማታይ ከምንም በላይ በአፍሪቃ ያሉ መሪዎች የአስተዳደር ብልሹነትን ማስወገድ አለባቸው ብለዋል። ሙስናን ሲታገሉና ሠብዓዊ መብትን ሲያከብሩ ያኔ አዲሱ የአሜሪካን ፕሬዚዳንት አፍሪቃን ይረዳሉ ሲሉም ገልፀዋል።