ከምርጫ ማግስት በቀረበው የሽግግር መንግስት ጥሪ እና ተቃዉሞ
ቅዳሜ፣ ሰኔ 26 2013ማስታወቂያ
ከምርጫ ማግስት በቀረበው የሽግግር መንግስት ጥሪ የኦነግ አመራሮች ውዝግብ
በአቶ አራርሶ ቢቂላ የሚመራው የኦሮሞ ነጻነት ግንባር “በኦሮሞ ፌዴራላዊ ኮንግረስና በኦሮሞ ነጻነት ግንባር ስም እየተሰራጨ ነው” ያለውን “የሽግግር መንግስት” አዋጅ እንደማይቀበል ገለፀ፡፡
ፓርቲው ባወጣው ባለሰፊ አተታ መግለጫው በአቶ ዳውድ ኢብሳ በሚመራው የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ይፋዊ ገፅ የወጣውን የሽግግር መንግስት ምክረ ሀሳብ ጥሪንም ነቅፎ አቋሙን ገልጾበታል፡፡
የፓርቲው ባለስልጣናት ለዶይቼ ቬለ በሰጡት ተጨማሪ ማብራሪያም ፓርቲያቸው ስልጣን በምርጫ እንዲተላለፍ ያምናል ብለዋል፡፡
ስዩም ጌቱ ከአዲስ አበባ ዘገባ ልኮልናል፡፡