1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ከሳውዲ አረቢያ የሚመለሱ ኢትዮጵያውያን

ሐሙስ፣ ታኅሣሥ 3 2006

የሳውዲ አረቢያ መንግስት ህገወጥ ስደተኞች ያላቸውን የውጪ ዜጎች ከኣገሩ ለማስወጣት በጀመረው መጠነ ሰፊ ዘመቻ አኩዋያ የኢትዮጵያ መንግስትም 30 000 ያህል ዜጎችን ወደ ኣገራቸው ለመመለስ መገደዱን ባለፈው ወር ማስታወቁ ይታወሳል።

https://p.dw.com/p/1AYBc
Saudi Arabien Riad Unruhen
ምስል AFP/Getty Images

ዓለም ዓቀፉ የስደተኞች ተቐም IOM ዛሬ እንዳስታወቀው ግን ባልተጠበቀ ሁኔታ እስከ ኣሁን ብቻ ይህ ቁጥር በአራት እጥፍ ጨምሮ 120 000 ያህል ኢትዮጵያውያን ወደ ኣገር ቤት ተመልሷል። ገና ደግሞ ኣልተጠናቀቀም። ይህም ይላል IOM በዓለማችን በቅርብ ጊዜ ታሪክ የመጀመሪያው ትልቁ የስደት ተመላሾች ቁጥር መሆኑ ነው። በመሆኑም በኢትዮጵያ የIOM የበላይ ኃላፊ የሆኑት ሚ/ር ኦጊና ጆይሳሽ እንደገለጹት እነዚህን ከስደት ተመላሾች ለማጘጘዝም ሆነ ለመንከባከብ ሁኔታው ከድርጅታቸው ኣቅም በላይ እየሆነባቸው ነው።እናም IOM የሌሎች ዓለም ዓቀፍ ተቐማትን ድጋፍ ለመጠየቅ ተገዷል። በዚሁ መሰረት ኣሁን ለኣስቸኩዋይ ጊዜ ድጋፍ 9,5 ሚሊየን ዩሮ ወይንም 247 ሚሊየን ብር ያስፈልጋል።b

London Heathrow Flugzeugbrand Ethiopian Airlines
ምስል Reuters

የተመላሾች ቁጥር በትንሹ 150 000 ገደማ ሊደርስ ይችላል ያሉት ሚ/ር ኦጊና የሚመጡት ደግሞ ባዶ እጃቸውን ከመሆኑም በላይ አብዛኞቹ የተጎሳቆሉ፣ የታመሙ፣ እና ህጻናትን የያዙ እንዲሁም የደረሱ ነፍሰጡሮች ጭምር በመሆናቸው የቁጥራቸውን ያህል ኣስፈላጊው ወጪም ባልተጠበቀ ሁኔታ እያሻቀበ መሆኑን ኣስረድቷል።

ዓለም ዓቀፉ የሰራተኞች ተቐም በምህጻሩ ILO እንደሚለው ደግሞ እነዚህ ከስደት ተመላሾች በዚያች ኣገር በነበሩበት ዓመታት ይህ ነው የማይባል ዓካላዊ እና ስነልቦናዊ በደል የደረሰባቸው ናቸው።

በሳውዲ አረቢያ ለአራት ዓመታት ያህል በአናጺነት ሲያገለግል የቆየው የ36 ዓመቱ ቀመር ዓሊም ህይወት በሳውዲ አረቢያ እያነቡ መኖር ነው ሲል ብሶቱን ገልጿል።

Paris Demo Einwanderer aus Äthiopien in Saudi Arabien
ምስል DW/H. T. Torode

ከአስር ወራት በፊት ነበር ለልጆቼ በተቻለ ፍጥነት ገንዘብ ለመላክ ኣስቤ ወደ ሳውዲ አረቢያ የሄድኩት ያለችው የ30 ዓመቷ ገንዘብ ተፈራ በበኩልዋ ስራ ጀምራ ግን ደሞዝዋን ለመከፈል ሰባት ወር እንዳቆዩዋት በምሬት ኣውስታለች።

ተበድሬ የሄድኩትን ገንዘብ እንኩዋን ከፍዬ ሳልጨርስ ነው የመጣሁት ያለችው ኣንዲት ሌላ ኢትዮጵያዊት ሴትም እዚህ የስራ እድል ባለመኖሩ ቢያንስ እዳዋን ከፍላ ከህሊናዋ ጋር ለመታረቅ ስትል ተመልሳ ወደ አረብ ኣገር ለመሄድ እያሰበች መሆንዋን ለIOM ኣስረድታለች። አብዛኞቹ ተመላሾችም ወደየቀበሌያቸው ከመመለስ ይልቅ በአዲስ ኣበባ መቆየትን ይመርጣሉ ተብሏል።

91 ሚሊየን ገደማ ህዝብ ባላት ኢትዮጵያ አዲስ አበባን ጨምሮ በከተሞች ያለው የስራ ኣጥነት መጠን 20 በመቶ ሲሆን በIOM መረጃ መሰረት የኣንድ ኢትዮጵያዊ ኣማካኝ ገቢ በቀን ከሁለት ዶላር በታች ነው።

ጃፈር ዓሊ

ነጋሽ መሃመድ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ