1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ከኢትዮጵያ የተባረረችው ጋዜጠኛ

ረቡዕ፣ ሰኔ 16 2002

ከኢትዮጵያ በአስቸኳይ እንድትወጣ የተደረገችው የአሜሪካ ድምፅ ራድዮ ጋዜጠኛ አንዳችም ጥፋት እንዳልፈፀመች አስታወቀች ። የምርጫ እና ሌሎች የኢትዮጵያ ዜናዎችን ለመዘገብ ከምርጫው ቀደም ብላ ኢትዮጵያ የገባችው ጋዜጠኛ ሂተር ሞርዶክ ለዶይቼቬለ እንደተናገረችው ለስራዋ አስፈላጊ የሆኑ ፈቃዶችን አግኝታለች ።

https://p.dw.com/p/O0dG
ምስል DW

ሆኖም ዘገባ ለማጠናቀር ወደ ሐረር በሄደችበት አጋጣሚ በአካባቢው ግጭት ስለመኖሩ የሰማችውን መረጃ ካጣራች በኃላ በፖሊስ ተይዛ ሰኔ 10 ,2002 ዓም ከኢትዮጵያ መባረሯን አስታውቃለች ። የዋሽንግተን ዲሲው ወኪላችን አበበ ፈለቀ ካይሮ ግብፅ የምትገኘዋን ጋዜጠኛ ሞርዶክን በስልክ አነጋግሮ ተከታዩን ዘገባ አጠናቅሯል ።

አበበ ፈለቀ ፣ ሂሩት መለሰ

አርያም ተክሌ