1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ከእስር የተፈቱት የሳዑዲ ልዑል ተናገሩ

ረቡዕ፣ መጋቢት 12 2010

በሳዑዲ ዓረቢያ የጸረ ሙስና ኮሚሽን ተጠርጥረው ለ83 ቀኖች  በቁጥጥር ስር የሰነበቱት የሳዑዲ ታላቁ ባለሀብት አል ወሊድ ቢን ጥላል ለአጎታቸው ንጉስ ሰልማንም ሆነ ለአልጋወራሽ መሀመድ ቢን ሰልማን በየትኛውም መንገድ ድጋፋቸውን እንደሚሰጡ አስታወቁ።

https://p.dw.com/p/2ui6n
Prinz Walid Ibn Talal
ምስል AP

የሳዑዲ ዓረቢያ ታላቁ ባለሀብት አል ወሊድ ቢን ጥላል

 ልዑሉ ከእስር ከተፈቱ ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ ከብሉምበርግ ቴሌቪዥን ጋር ባደረጉት ቃለ መጠይቅ በደረሰባቸዉ የያዙትም ቂም እንደሌለ እና ለንጉሱም ሆነ ለአልጋ ወራሹ ይቅርታ ማድረጋቸውን ተናግረዋል። ዎል ስትሬት ጆርናልን ጨምሮ በርካታ መገናኛ ብዙሃን ስድስት ሚሊየን ዶላር ከፍለው ነው የተለቀቁት ብለው ቢዘግቡም እሳቸዉ ግን ምንም የከፈሉት እንደሌለ አጽንኦት ሰጥተዋል። በግላቸው ከንጉሱም ሆነ ከአልጋ ወራሹ ጋር ሚስጢራዊ ስምምነት ማድረጋቸውን ይፋ ያደረጉት ልዑል ወሊድ ቢንጥላል ዝርዝር ሁኔታዎችን ለማብራራት ግን እንደማይፈልጉ ነዉ ያሳወቁት። ከሪያድ ስለሺ ሽብሩ ከሪያድ ተከታዩን ዘገባ ልኮልናል።

ስለሺ ሽብሩ

ሸዋዬ ለገሠ

ኂሩት መለሰ