1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ኬንያና እንግሊዛዊቷ አሸባሪ፤

ሐሙስ፣ መስከረም 16 2006

ኬንያ፤ በመዲናዋ በናይሮቢ ዌስትጌት በተባለው ግዙፍ የገበያ ህንጻ ውስጥ ፣ባለፈው ሳምንት ቅዳሜ፣ በሶማልያው አሸባብየአሸባሪዎች ቡድን፤ ቢያንስ72 ሰዎች ከተገደሉ ወዲህ ፣የ 67 ቱ ሰለባዎች የቀብር ሥነ ሥርዓት ተፈጽሟል ። የ3 ቀን የኀዘን ጊዜም ታውጆ ተግባራዊ በመሆን

https://p.dw.com/p/19p9q
ምስል Reuters

ላይ ሳለ፣የዩናይትድ እስቴትስ፤ የብሪታንያ፤ የአሥራኤልና የሌሎችም ጠበብት ከኬንያ የምርመራ ጠበብትጋር በመተባበር፤ አደጋው እንዴትሊሠነዘር እንደቻለ በማጣራት ላይ መሆናቸውታውቋል። 40 ሚሊዮን ኑዋሪዎች ባሏት ኬንያ የሙስሊሞች ቁጥር 10 ከመቶ ገደማ ሲሆን፣ ተገቢ ቁጥጥር በማይደረግበት ድንበር፤ ሠርገው የሚገቡ የአሸባብ ታጣቂዎች ከአንዳንድ ኬንያውያን የእምነት ተጋሪዎቻቸው ድጋፍ እንዳልተለያቸው ተነግሯል። አሸባብ ፤ ሶማሌዎችን ብቻ ሳይሆን የተለያዩ ሃገራት ተወላጆችንም ማሰለፉ ይነገርለታል። ከእነዚህም አንዷ ሳምንታ የተባለችው እንግሊዛዊት መሆኗ ታውቋል። ይህች ሴትዮ እንዴት በሽብር ተግባር ለመሰማራት ተነሳሳች? የለንደኑን ዘጋቢአችንን ድል ነሣ ጌታነህን በስልክ ጠይቄው ነበር።

ድልነሣ ጌታነህ

ተክሌ የኋላ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ