1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ኬንያ ናይሮቢ የደረሰዉ ጥቃት

ሰኞ፣ መስከረም 13 2006

በኬኒያ መዲና ናይሮቢ ካሉት ግዙፍ እና ዘመናዊ የገበያ ማእከላት ኣንዱ እና ምናልባትም ዋንናው የሆነው WEST GATE የገበያ ማእከል ቅዳሜ እና እሁድን ጨምሮ በሳምንት ለሰባት ቀናት ከጡዋቱ 2 ሳዓት እስከ ምሽቱ 2 ሳዓት ለደንበኖቹ ክፍት ነበር

https://p.dw.com/p/19miL
A police officer tries to secure an area inside the Westgate Shopping Centre where gunmen went on a shooting spree in Nairobi September 21, 2013. The gunmen stormed the shopping mall in Nairobi on Saturday killing at least 20 people in what Kenya's government said could be a terrorist attack, and sending scores fleeing into shops, a cinema and onto the streets in search of safety. Sporadic gun shots could be heard hours after the assault started as soldiers surrounded the mall and police and soldiers combed the building, hunting down the attackers shop by shop. Some local television stations reported hostages had been taken, but there was no official confirmation. REUTERS/Siegfried Modola (KENYA - Tags: CIVIL UNREST)
ምስል Reuters

ካለፈው ቅዳሜ ቀትር ላይ ጀምሮ በእርግጥ የገበያ ማእከል ሳይሆን የጦር ሜዳ ሆኖ ነው የሰነበተው። ድንገት ወደማእከሉ ዘልቀው ከየኣቅጣጫው ተኩስ የከፈቱት በቅጡ የታጠቁ ኣሸባሪዎች በቁጥር ከ 15 እስከ 20 ይሆናሉ ተብለዋል እስከ ኣሁን በሮይተርስ ዘገባ መሰረት የሙዋቾች ቁጥር 70 ደርሰዋል የቆሰሉ ደግሞ ከ 200 በላይ ተቆጥረዋል የኬኒያ ፖሊስ እና የጦር ኃይሉ ከበባውን ኣጠናክሮ እና ወደ ውስጥ ዘልቆ በኣንድ በኩል በህይወት ያሉ ሰላማዊ ሰዎችን ለመታደግ እና ገዳዮችን ለመያዝ ኣሊያም ለመግደል የቻለውን ሁሉ ሲያደርግ ቆይተዋል ኣሁንም ድረስ ግን ኣላጠናቀቀም ምክኒያቱም ከጥቃቱ ለመደበቅ በላያቸው ላይ የዘጉትን ጨምሮ በተለያዩ ጉራንጉሮች የተደበቁም ስላሉ የኬኒያ የውስጥ ጉዳይ ካቢኔ ጸኃፊ ዮሴፍ ኦሌ ሌንቁ እንደሚሉት ወታደራዊው እርምጃ መካሄድ ያለበት በጥንቃቄ ነው።
የኬኒያው ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬኒያታ ጥቃቱን ኣስመልክተው ለህዝባቸው ባሰሙት ንግግር ከዘግናን አረመኔያዊ ድርጊታቸው ጋር ተደብቀው ኣያመልጡም ኣይቀጡ ቅጣት እንቀጣቸዋለን ብለዋል
«የኬኒያ ተቃዋሚ ፓርቲዎች መሪዎችም ኣስቸኩዋይ ስብሰባ ኣድርገውድርጊቱን ኮንነዋል በእንዲህ ኣይነቱ ጊዜ ኣሉ የቀድሞው የኬኒያ ጠ/ሚ ራይላ ኦዲንጋ የተቃዋሚ መሪዎችን በመወከል በእንዲህ ኣይነቱ ጊዜ በጋራ ሆነን በተቀናጀ መልኩ በሁኔታው ላይ መረባረብ ይኖርብናል»

Smoke rises over Westgate shopping centre after an explosion in Nairobi, September 23, 2013. Powerful explosions sent thick smoke billowing from the Nairobi mall where militants from Somalia's al Qaeda-linked al Shabaab group threatened to kill hostages on the third day of a raid in which at least 59 have already died. REUTERS/Karel Prinsloo (KENYA - Tags: CIVIL UNREST CRIME LAW) ***FREI FÜR SOCIAL MEDIA***
ምስል Reuters

«በከተማይቱ ናይሮቢ ዋና ዋና ሆስፒታሎች ያሉ ኃኪሞችም በጋራ ቁስለኖችን ለማትረፍ እየተረባረቡ ነው በሺዎች የሚቆጠሩ ኬኒያውያንም የቁስለኖችን ህይወት ለመታደግ ደም ለመለገስ ተሰልፈዋል የሆስፒታል ምንጮች እንደሚሉት ደግሞ ቁስለኖቹ በኣብዛናው የቤተሰብ አባላት ናቸው ባል እና ሚስት እናት እና ልጆች ሌላም ሌላም ምክኒያቱም WEST GATE የገበያ ማእከል የናይሮቢ ሸማቾችም ሆኑ እንግዶች በግልም ሆነ በጋራ በተለይም ቅዳሜ እና እሁድ እየተዝናኑ ለመሸመት ጭምር የሚያዘወትሩበት ታዋቂ እና ምቹ የገበያ ማእከል ነው በእንዲህ ኣይነቱ ስፍራ ባልተጠበቀ ሳዓት የተቀነባበረ ተኩስ ቢከፈትም ቅዳሜ ከሳዓት በሁዋላ ከ 1000 በላይ ሰላማዊ ሰዎች በሰላም ከማእከሉ ለመውጣት ችለዋል ከውስጥ ያመለጡ የዓይን እማኖች እንደሚሉት ተኩዋሾቹ እስላም ባልሆኑ እና በተለይም በውጪ ሰዎች ላይ ያተኮሩ ነበሩ እስከ ኣሁን ትክክለናው ቁጥር ባይታወቅም ከሚዋቾቹ መካከል ሶስት ያህሉ የእንግሊዝ ዜጎች መሆናቸው ተሰምተዋል»
ኬኒያ ከኣልሸባብ ኣንጻር ስጋት ውስጥ የገባችው የዛሬ 2 ዓመት ወደዚያች ኣገር ግዛት ዘልቃ በቡድኑ ላይ ወታደራዊ ጥቃት ከጀመረች ወዲህ ነው በእርግጥ ያኔም ቢሆን ባለስልጣናቱ እንደሚሉት የኬኒያ ጦር ወደ ሶማሊያ የዘመተው ኣልሸባብ በኬኒያ ምድር የውጪ ጎብኒዎችን እና የእርዳታ ሰራተኖችን በማገት እና በመግደል የሚያደርሰውን የሽብር ጥቃት ለመበቀል ወይንም ለመከላከል ነበር።
የናይሮቢው ጥቃት እንደተሰማ የብሪታኒያ የውጪ ጉዳይ ሚ/ር ን ጨምሮ በዓለም ዙሪያ ያሉ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እና የመንግስታት መሪዎችም አድራጎቱን በእጅጉ ኮንነዉታል የኣሜሪካው ፕሬዝዳንት ባራክ ኦባማም ትላንት እሁድ ለኬኒያው ኣቻቸው ኡሁሩ ኬኒያታ ስልክ ደውለው የኣልሸባብን ጥቃት ለመከላከል በተለይም እነዚህን ኣሸባሪዎች ለፍርድ ለማቅረብ ኣገራቸው ከኬኒያ ጎን እንደምትቆም ኣረጋግጠውላቸዋል
የኦጋዴን ነጻ ኣውጪ ግንባር ONLF ም በተለይ በሰላማዊ ሰዎች ላይ የሚፈጸመውን ጥቃት በማውገዝ መግለጫ ኣውጥተዋል ለኬኒያ ህዝብ እና መንግስት በጉዳዩ ማዘኑን የገለጸው ONLF የሶማሌ ህዝብም በማንናውም መልኩ በሰላማዊ ሰዎች ላይ ጥቃት የሚሰነዝሩ ኃይሎችን በማግለል ረገድ አቁዋም እንዲዪዝ ጥሪ ኣድርገዋል በኬኒያ የሚኖሩ የሶማሊያ ማህበረሰብ ኣባላትም በጉዳዩ ማዘናቸውን በመግለጽ የሽብር ተግባርን እያወገዙ መሆናቸው ተዘግበዋል።
«የታጠቁ አሸባሪዎች በቡድን ሆነው በናይሮቢ መናፈሻ አካባቢ ወደሚገነው WEST GATE የገበያ ማእከል በኃይል በመግባት በሰራተኖች እና ደንበኖች ላይ ትርጉም የለሽ ጥቃት ሰንዝረዋል እናም ብርካቶችን ገድለው ጥቂት የማይባሉትን ኣቁስለዋል እና እንደ መንግስት እና ኣገር ከሰለባዎቹ ቤተሰቦች ጋር እንቆማለን እያንዳንዱ ኬኒያዊ ከጎናቸው እንዲቆምእጠይቃለሁ እግዝኣብሄርም ከሀዘኑ መጽናናትን እንዲሰጣቸው እለምናለሁ ይህ ኣሳዛን ነገር ነው እንዲሁም በግል ምን እንደሚሰማችሁ ይገባናል በጣም የቅርብ ዘመድ የሆኑ የቤተሰብ አባላትን ኣታቸዋል።
የተወሰኑ ሰዎች ኣሁንም ድረስ እዚያው በህንጻው ውስጥ ይገናሉ የጸጥታ ኃይላችንም ከሁኔታው ጋር በመንቀሳቀስ ላይ ነው እነዚያን ኣሁንም ድረስ በአደጋ ውስጥ የሚገኑትን ዜጎች ለመታደግ ደግሞ መደራደርም ኣስፈላጊ ነው ቁጥሩም በእርግጥ ገና ኣልታወቀም የተወሰኑ ሰዎች በኣንደና ፎቅ እና በምድር ቤት ይገናሉ አሸባሪዎቹም እስከ ኣሁን እየተፈታተኑ ንው እንደሚታወቀው ሁንታው በጸጥታ ኃይላችን እጅ ተይዘዋል እርግጥ ሁኔታው በእነሱ እጅ እንዲቆይ እንፈልጋለን።

A helicopte and birds fly above as a plume of black smoke billows rising over the Westgate Mall, following large explosions and heavy gunfire, in Nairobi, Kenya Monday, Sept. 23, 2013. Four large blasts rocked Kenya's Westgate Mall on Monday, sending large plumes of smoke over an upscale suburb as Kenyan military forces sought to rescue an unknown number of hostages held by al-Qaida-linked militants. (AP Photo/Riccardo Gangale) ***FREI FÜR SOCIAL MEDIA***
ምስል picture-alliance/AP

ጃፋር አሊ

ተክሌ የኋላ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ