ወታደራዊው ጁንታና ውጥረት በጊኒ
ዓርብ፣ ታኅሣሥ 17 2001ማስታወቂያ
የጊኒ የቀድሞ መንግስት ባለስልጣናት የተሰጣቸው የሃያ አራት ሠአታት ቀነ ገደብ ሳይገባደድ ዛሬ ለወታደራዊው ጁንታ መግባታቸውን አዣንስ ፍራንስ ፕሬስ ዘገበ።ጊኒን ለሃያ አራት አመታት በአምባገነንነት ሲገዟት ቆይተው ባለፈው ሰኞ ያረፉት የቀድሞው ፕሬዚዳንት ላንሳና ኮንቴ ዜና ረፍትን ተከትሎ ወታደራዊ ጁንታ የአመራሩን ቁንጮ መቆጣጠሩን ገልፆ እንደነበር ይታወቃል። የቀድሞ የመንግስት ባለ ስልጣናት ዛሬ ዋና ከተማዋ ኮናክሬ ተገኝተው የጁንታው መሪ ሻለቃ ሞሳ ዳዲስ ካማራን ፕሬዚዳንት ማለታቸውም ታውቓል።