1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ወደ ሰሜን ሸዋ የተዛመተው ግጭት

ሰኞ፣ መጋቢት 30 2011

ከሰሞኑን በሰሜን ሸዋ ዞን አጣዬ አካባቢ የተፈጠረው ግጭት  የበርካታ ሰዎች ሞት እና የንብረት ውድመት ማስከተሉን የሰሜን ሸዋ ዞን አስታወቀ፡፡ በተጠቀሰው አካባቢ ለሚታየው የሰላም መናጋትም የኦሮሞ ነፃ አውጭ ግንባር በአጭሩ  ኦነግ የተባለው ኃይል ተጠያቂ መሆኑንም ዶይቼ ቬለ DW ስለሁኔታው የጠየቃቸው ባለስልጣን አመልክተዋል።

https://p.dw.com/p/3GT82
20.06.2013 DW Online Karten Basis Aethiopien spanisch

«ጥቃት አድራሹ ኦነግ ነው»

 የቡድኑ እንቅስቃሴ አስቀድመው ለበላይ አካላት ማሳወቃቸውን የጠቆሙት የሰሜን ሽዋ ዞን የአስተዳደርና ፀጥታ ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ አቶ ካሳሁን እምቢያለ ለድርጊቱ ተጠያቂዎችን ለይቶ ይፋ ከማድረግ ይልቅ በጥቅሉ አንዳንድ የጥፋት ኃይሎች እየተባለ መድበስበሱ መፍትሄ እንዳላመጣ ገልጸዋል። የባሕር ዳሩ ዘጋቢያችን ዘገባ ልኮልናል።

ዓለምነው መኮንን

ሸዋዬ ለገሠ

ነጋሽ መሐመድ