1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ዋሪስ ዲሪ በበርሊን የከፈቱት የህክምና ማዕከል

ማክሰኞ፣ መስከረም 7 2006

በሶማሊያ የተወለዱት የሴቶች ተሟጋች እና ሞዴል ዋሪስ ዲሪ ባለፈው ረቡዕ የሴት ልጅ ግርዛት ሰለባ የሆኑ የሚረዱበት «ዴዘርት ፍላወር ሴንተር» የተባለ ማዕከል በርሊን ውስጥ መርቀው ከፍተዋል።

https://p.dw.com/p/19iRP
Waris Dirie, somalische Bestsellerautorin ("Wüstenblume") und Aktivistin gegen Genitalverstümmelung, kommt am 11.09.2013 als Schirmherrin zur Eröffnung des "Desert-Flower-Centers" am Krankenhaus Waldfriede in Berlin an. Es ist das europaweit erste Krankenhaus, das von Genitalverstümmelung betroffenen Frauen psychologisch und chirurgisch hilft. Die WHO geht davon aus, dass derzeit täglich tausende Mädchen bei der sogenannten rituellen Beschneidung verstümmelt werden, jedes vierte sterbe an den direkten oder langfristigen Folgen des Eingriffs. Foto: Stephanie Pilick/dpa
Berlin Eröffnung Desert-Flower-Center Krankenhaus Waldfriedeምስል picture-alliance/dpa

በየl1 ሰከንዱ አንድ ለአቅመ አዳም ያልደረሰች ልጅ ትገረዛለች። ይህም በሹል ድንጋይ፣ በቢለዋ ተሻለ ቢባል በምላጭ ወይም በመቀስ መሆኑ ነው። የጎጂ ልማዱ አፈፃፀም እንደየ ሀገሩ ይለያያል። በከፊል ወይንም ሙሉ በሙሉ የመዋለጃ አካላቸዉ የሚተለተልበት፣ ከዚህም አልፎ ትንሽዬ ቀዳዳ ብቻ ለሽንት ተትቶ ሙሉ በሙሉ የሚሰፋበት አጋጣሚ አለ። በብዛት በአፍሪቃ በመካከለኛው ምስራቅ እና እስያ የሚፈፀመውን Female Genital Mutilation FGM ይሉታል። አብዛኛውን ጊዜ እድሜያቸው ከ4-7 ባልበለጡ ህፃናት ላይ ይረፀማል። ኃላም እድሜ ልክ የሚቆይ ህመም እና ትውስታ ይዘው ይኖራሉ። በዚህ የተነሳም የFGM ሰለባዎች በቀዶ ጥገና ለማከም ሀኪሞች መንገድ ፈጥረዋል። በዓይነቱ የመጀመሪያ በሆነው እና በዋሪስ ዲሪ ድጋፍ ባለፈው ሳምንት በበሊን ከተማ የተከፈተው የህክምና ማዕከል በጀርመን የሚኖሩ ቁጥራቸው ከ25,000 እስከ 50,000 የሚደርሱ ህፃናት እና አዋቂዎች ሊረዱ ይቻላል ተብሎ ይገመታል። በህክምና ማዕከሉ ጋዜጠኛ ናዎሚ አግኝታ ካነጋገረቻቸው ውስጥ ሰናይት አንዷ ናት።

Senait Demisse, Patientin im Krankenhaus Waldfriede, wo von heute an OPs für Opfer von Genital-Verstümmelungen durchgeführt werden, Foto: DW/Naomi Conrad, Bonn, 11.09.2013
ሰናይት በዴዘርት ፍላወር የህክምና ማዕከልምስል DW/N. Conrad

« ትንሽዬ ልጅ ነበርኩ። በትክክል አላስታውስም የ7 ወይም የስድስት ዓመት ልጅ ሳለሁ ነበር። ትላለች ሰናይት። የሀኪም ቤት አልጋ ጠርዝ ላይ ቆማ ቀዶ ህክምና የምታደርግበትን ሰዓት እየጠበቀች፤ ያኔ ስለገጠማት ታወራ ጀመር። የሰፈሩ ሰው ሁሉ ተሰብስቦ ምግብ እና ፌስታ ነበር። ሰናይት ሁለት ጓደኞቹ ሲገረዙ የፈሰሳቸውን ደም እና ለማምለጥ የሞከረችው ትዝ ይላታል።«ከዛ ያዙኝ። የሆነውን ሁሉ በደንብ አላስታውስም። ፤ ናዎሚ፣ መቼም በጣም ህመም ነበረው አይደል? ስትል ትጠይቃለች።« አላስታውስም። ምናልባት አእምሮዬን ስቼ ነበር። ከዛ በኋላ ስለሆነው ነገር ምንም አላስታውስም።»

የ 34 ዓመቷ ሰናይት ከጥቂት ወራት በፊት ነው አዲስ ስለሚከፈተው የህክምና ማዕከል የሰማችው። እንደ እሷ ሙሉ በሙሉ የመዋለጃ አካላቸዉ የተተለተለ እና ከዚህም አልፎ ትንሽዬ ቀዳዳ ብቻ ለሽንት መሽኛ ተትቶ ሙሉ በሙሉ ብልታቸው የተሰፋ ልጃ ገረዶች ፤ ሲያድጉ በግብረ ስጋ ግንኙነት ወቅት ወይም ልጅ ሲወልዱ አስከፊ ችግር ይገጥማቸዋል። ስለሆነም ሰናይት ወዲያው ነው ከምትኖበት ፖላንድ ወደዚህ ጣቢያ ለመምጣት የወሰነችው። « የተሟላ ሰው መሆን እፈልጋለሁ። የቆረጡብኝ እንዲመለስልኝ እፈልጋለሁ» ቀዶ ህክምናዋ ለሚቀጥለው ቀን ተዛውሯል። ብዙም አልፈራም ትላለች ሰናይት። ሀኪሟ ዶክተር ሮላንድ ሼረር ግን ጉዳይዋን በጥንቃቄ ይመለከቱታል።« ሁኔታው ከተፈፀመ በኃላ ጊዜው በራቀ ቁጥር በርግጥ ቀዶ ህክምና ቀላል አይሆንም። ደረቅ ጠባሳ ነው የሚኖረው ስለዚህ ይህ ቀዶ ህክምና በሚከናወንበት ጊዜ የተወሰነ ልምድን ይጠይቃል።»

Bildnummer: 60456807 Datum: 10.09.2013 Copyright: imago/epd Roland Scherer, Chefarzt und Experte für Darm- und Enddarmchirurgie am Berliner Klinikum Waldfriede, am Dienstag (10.09.2013) vor einem Transparent zur Eröffnung des Desert Flower Centers in der Klinik. In Zusammenarbeit mit der Desert Flower Stiftung wird am Mittwoch (11.09.13) in Waldfriede ein Zentrum eröffnet, das Frauen aufnimmt, die beschnitten sind und sich nun einem Eingriff unterziehen wollen, um von den Qualen erlöst zu werden. Europaweit ist es nach Angaben der Stiftung die einzige Anlaufstelle dieser Art. Weltweit leiden 125 Millionen Frauen an den Folgen der weiblichen Genitalverstümmelung. (Siehe epd-Meldung vom 10.09.2013) Berliner Krankenhaus bietet Hilfe für beschnittene Frauen Gesellschaft Pressetermin Shooting xdp x1x 2013 quer premiumd arzt Beschneidung Frauen Gesellschaft Gesundheit Klinik Krankenhaus Medizin Personen weiblich o00 Wüstenblume 60456807 Date 10 09 2013 Copyright Imago epd Roland Scherer Chief doctor and Expert for Intestine and at Berlin Hospital Waldfriede at Tuesday 10 09 2013 before a Transparent to Opening the Desert Flower Centers in the Clinic in Cooperation with the Desert Flower Foundation will at Wednesday 11 09 13 in Waldfriede a Center opens the Women up the curtailed are and to now a Intervention subjected want to from the Agony ERLÖST to will Europe is it after Information the Foundation the only one Stop this one Art worldwide suffer 125 Million Women to the Follow the female Genital mutilation See epd Message of 10 09 2013 Berlin Hospital offers Help for Trimmed Women Society Press call Shooting XDP x1x 2013 horizontal premiumd Doctor Circumcision Women Society Health Clinic Hospital Medicine People female o00 Desert flower
ዶክተር ሮላንድ ሼረር አዲስ በዋሪስ ዲሪ አማካኝነት የተከፈተውን ማዕከል በኃላፊነት ይመራሉ።ምስል imago/epd

ዶክተር ሮላንድ ሼረር አዲስ በዋሪስ ዲሪ አማካኝነት የተከፈተውን ማዕከል በኃላፊነት ይመራሉ። ማዕከሉ የህክምና እና የስነ ልቦናዊ አገልግሎት ይሰጣል። ከዛም በተጨማሪ «ዴዘርት ፍላወር ሴንተር» የማነቃቃት ስራ ያካሂዳል። ሼረር የመልሶ ጥገናውን ህክምና ከሚያደርጉት ሀኪሞች ይመደቡ እንጂ በርካታ ሀኪሞች በዚህ ረገድ ተገቢውን ስልጠና እንዳላገኙ ከአህን ዮንቨርሲቲ ዳን ኦዴይ ያብራራሉ። « ቀድመው በማህፀን ሀኪሞች አማካኝነት ቀዶ ህክምና የተደረገላቸው ምን ያህል ሴቶችን እኔ እንደገና ቀዶ ህክምና እንዳደረኩ መገመት ይዳግተዎታል። »

በአግባቡ ያልተካሄደ ቀዶ ህክምና የታካሚዎቹ ሌላ ሁለተኛ ስቃይ እንደሆነ ኦዴይ በብስጭት ይገልፃሉ። ስኬታማ በሆነ ቀዶ ህክምና የታካሚዎቹን የወሲብ ፍላጎት ማሻሻል እና የሙሉነትን ስሜት በማዳበር በራስ መተማመንን ማጠንከር እንደሚቻል ይገልፃሉ። ሰናይት እንድ ቀን እንደ ዋሪስ ዲሪ ይህን ጎጂ ልማድ ለማስቆም ተሟጋጅ መሆን እንደምትፈልግ ለናዎሚ አጫውታታለች።« ከሆነ ጊዜ በኋላ ወደ ሀገሬ ተመልሼ ማስተማር እፈልጋለሁ። ልጆችን ከዚህ ለማዳን ሰው ሊገርዛችሁ ሲመጣ ፖሊስ ጥሩ እላቸዋለሁ። ያኔ ልጆቹም በታገል ይጀምራሉ።»

Das Filmplakat zu "Wüstenblume" nach dem gleichnamigen Bestseller von Waris Dirie, Regie: Sherry Hormann, in der Hauptrolle Liya Kebede. Der Film behandelt u.a. weibliche Genitalverstümmelung, Kinostart 24.9.2009. © Majestic !!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!Permission is granted to newspapers and periodicals to reproduce these press materials in articles publicizing the distribution of the Motion Picture. All other use is strictly prohibited, including sale, duplication, or other transfer of this material. © 2009 Majestic Film Verleih GmbH". !!!!!!!!!!!!!!!!!!
የዋሪስ ዲሪ መፅሀፍምስል Majestic

እንደ ሰናይት ምኞት ልጆቹ ፖሊስ መጥራት መቻላቸው አጠራጣሪ ነው። በብዛት ልጆቹ ገና በልጅነት እድሜያቸው ነው የሚገረዙት። ነገር ግን ችግሩን ይፋ ያደረጉ እንደ ዋሪስ ዲሪ ያሉ የሴት ልጅ የመብት ተሟጋቾች አሉ። ዲሪ ገና የ4 ዓመት ልጅ ገደማ ሳሉ መገረዛቸውን ባሳተሙት መፅሐፋቸው አስፍረዋል። እንደ „ Terre des Femmes“ የተሰኘው የርዳታ ድርጅት ከሆነ ጀርመን ውስጥ ከ24 000 የሚበልጡ ሰለባዎች ይገኛሉ። ወደ 5 ሺ የሚጠጉ እንደውም እጅግ አስጊ ሁኔታ ላይ ይገኛሉ። እንደ የበርሊን የህግ ጉዳይ ተመልካች የምክር ቤት አባል ፦ ቶማስ ኃይልማን ከሆነ የጀርመን ፖለቲካ የሚገርዙ የግለሰብ ክሊኒኮችን መከታተል፣ ጠንካራ የወንጀል ህግ ማውጣት እና ወንጀል መከታተል እንደሚገባው ይገልፃሉ። የብዙ ሴቶችን ህይወት ከዚህ ስቃይ ለማስቆም ዋንኛው መንገድ ወንጀለኞችን የማጋለጡ ስራ ነው። በዚሁ በጀርመን ለአቅመ አዳም ያልደረሱ ሴት ልጆችን የሚገርዙ ሀኪምን በማጋለጥ እና ማስረጃ ለማሰባሰብ የተባበሩ አንድ ሰው የሆነውን እንዲህ ያስረዳሉ።

የሴት ልጅ ግርዛት ጀርመን ውስጥ የራሱ የሆነ የወንጀለኛ መቅጫ አንቀፅ አይኑረው እንጂ በህግ ያስቀጣል። በፈረንሳይም እንዲሁ የወንጀሉ ቅጣት ከፍተኛ ነው፣ ልጃቸውን የሚያስገርዙ ወላጆች ከ10-30 አመት እስራት ይቀጣሉ ወይንም ወደ ትውልድ አገራቸው እንዲመለሱ ይደረጋሉ ።ይሁንና በድብቅ የማይሆን ነገር የለም።

የሴት ልጅ ግርዛት በአፍሪቃ፣ በመካከለኛው ምስራቅ እና በእስያ ብቻ ሳይሆን በአውሮፖ በሚኖሩ መጤዎች ምክንያትም መፍትሄ የሚሻ ጉዳይ ሆኗል። ምንም እንኳን የ«ዴዘርት ፍላወር ሴንተር» ለአቅም አዳም ያልደረሱ ልጆችን ከማስገረዝ ለማስቆም ባይችልም፤ የጎጂ ልማዱ ወንጀል የደረሰባቸውን ሰዎች ከእድሜ ልክ ህመምን ለማስቆም ስራውን ጀምሯል።

ልደት አበበ

ተክሌ የኋላ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ