1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ዓለም አቀፍ የወጣቶች ቀን እና ወጣቱ

ዓርብ፣ ነሐሴ 15 2007

በዓለማችን አብዛኞቹ ክፍሎች በነሐሴ ወር የሚከበረው ዓለም አቀፍ የወጣቶች ቀን ኢትዮጵያ ውስጥም ተከብሩዋል። ይህ የወጣቶች ዓለም ዝግጅት ርዕስ ነው።

https://p.dw.com/p/1GHzg
Bildergalerie Afghanistan Jugend Freestyle Parkour
ምስል picture-alliance/AFP Photo/W. Kohsar

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የጎርጎሮሳዊውን ነሐሴ 12 ቀን የዓለም አቀፍ የወጣቶች ቀን በማለት ሰይሟል። አላማው ወጣቱን ይበልጥ በማህበረሰቡ ዘንድ ማሳተፍ እና ተሰሚነት እንዲያገኝ ማድረግ ነው።በርካታ ሀገራት በሚያስቡት በዚህ ዓመታዊ ቀን፤ ወጣቶች ለዓለም የሚያበረክቱትን አስተዋፅዎ፣ የሚያስተዋውቁ፣ ጉባኤዎች ይካሄዳሉ። የስፖርት እና የባህል አውደ ርዕዮች ይዘጋጃሉ። ቀኑ ዘንድሮም ኢትዮጵያ ውስጥ ጉዳዩ በሚመለከታቸው የተለያዩ አካላት ታስቧል።

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ወጣት የሚላቸው እድሜያቸው ከ 15- 24 ክልል ውስጥ የሚገኙትን ነው። ከነዚህም አብዛኞቹ ወጣቶች የሚኖሩት እንደ ኢትዮጵያ ባሉ አዳጊ ሀገራት ነው። የዓለም አቀፍ የወጣቶች ቀን የሚለው ሀሳብ የተፀነሰው እኢአ በ1991 ዓም አውስትሪያ- ቪዬና ውስጥ በተካሄደው የተባበሩት መንግሥታት የአለም የወጣቶች መድረክ ላይ በተሳተፉ ወጣቶች ነበር።የዘንድሮውን የዓለም የወጣቶች ቀን ምክንያት በማድረግ የተባበሩት መንግሥታት ዋና ፀሀፊ ባን ኪ ሙን « የወጣቱ ተሳትፎ ከመጪውም በላይ ትልቅ ዋጋ አለው» የሚል መልዕክት አስተላልፈዋል። ወጣቱ ይህን ያህል ሚና የሚጫወት ከሆነ ደግሞ ፤ ፍላጎቱን የመግለፅ፣ የመሳተፉ ፣ የመወሰን መብት ሊከበርለት ይገባል። ከማህበረሰቡ 40 ከመቶ በላይ ወጣት በሆነበትስ ኢትዮጵያ ወጣቱ ምን ያህል ተደማጭነት አለው? ጥቂት ወጣቶችን አነጋግረናል።

Symbolbild Internationaler Friedenstag der UN
ምስል picture-alliance/ dpa

በኢትዮጵያ ሴቶች፣ህፃናት እና ወጣቶች ጉዳይ ሚኒስቴር የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ዳሬክተር አብይ ኤፍሬም፤ ዘንድሮ ዓለም አቀፍ የወጣቶች ቀን በኢትዮጵያ እንዴት እንደተከበረ ገልፆልናል። ዘገባውን በድምፅ ያገኛሉ።

ልደት አበበ

ሂሩት መለሰ