1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ዓለም ዓቀፍ የመገናኛ ብዙሃን መደረክ ተጠናቀቀ

ዓርብ፣ ግንቦት 28 2001

ዶቼ ቬለ ያዘጋጀዉ ለሦስት ቀናት የዘለቀዉ ዓለም ዓቀፍ የመገናኛ ብዙሃን መድረክ ዛሬ ተጠናቀቀ። ከአንድ መቶ አገራት የተዉጣጡ በተለያዩ የመገናኛ ብዙሃን ዘርፍ የሚሰሩ ጋዜጠኞችን ያገናኘዉ ይህ ጉባኤ በበዘርፈ ብዙ የመገናኛ ብዙሃን ጠቀሜታ ዙሪያ ተወያይቷል።

https://p.dw.com/p/I4Cl
ኤሪክ ቤተርማን የዶቼ ቬለ ሥራ አስኪያጅ

በጋዜጠኝነት አዘጋገብ ወዳጅ ጠላት የሚባል መኖር የለበትም በሚለዉ የዉይይት ነጥብም ግጭትን ከማባባስ መቆጠብ ከሙያዉ ስነምግባር ዋነኛዉ መሆኑ ተመልክቷል። ከጉባኤዉ ተሳታፊዎች መካከል በዘመናዊዉ ቴክኒዎሎጂ ማለትም ኢንተርኔት ንዑሳን ገፆች ላይ ማኅበረሰባቸዉን የሚጠቅም ተግባር የፈፀሙ ድንበር አልባ ጋዜጠኞች የሚል ሽልማት ከዶቼ ቬለ ተበርክቶላቸዋል።

ሸዋዬ ለገሰ/ተክሌ የኋላ