1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ዓለም ዓቀፍ ፀረ-ባርነት ቀን

ሰኞ፣ ኅዳር 23 2006

የዚህ ቀን በዓ/ዓቀፍ ደረጃ ታስቦ መዋሉ በተመድ መግለጫ መሰረት ከሰው ልጅ ታሪካፍ ፈተናዎች ኣንዱ የነበረው የባርያ ንግድ የተወገደበትን ኣሉታዊ ኣሻራ ለማስታወስ እና ከዚሁ ጎን ለጎን ዘመናዊ ባርነት እየተባሉ የሚታወቁትን የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ለመታገል ነው። ታህሳስ 2 ይላል ዛሬ የ ተመድ ዋ/ጸኃፊ ኮፊ ኣናንን ጠቅሶ የወጣው የድርጅቱ

https://p.dw.com/p/1ARwW
GettyImages 142001912 JERUSALEM, ISRAEL - MARCH 28: (ISRAEL OUT) Men help remove messages and prayers written by thousands of people addressed to God from the cracks in the Western Wall in preparation for the up coming Jewish Passover holiday on March 28, 2012 in Jerusalem's old city, Israel. All the notes once collected will be buried in a special place at the Mount of Olives.according tro Jewish law. Passover begins in the evening of Friday, April 6 and commemorates the story of the Exodus where the ancient Israelites were freed from slavery in Egypt. (Photo by Uriel Sinai/Getty Images)
ምስል Getty Images

መግለጫ የ ተመድ ጠ/ጉባዔ የባርነት ማስወገጃ ድንጋጌን መቀበሉን ያመለክታል። የሰዎች ህገወጥ ዝውውር የሚያስከትላቸውን ቀውሶች እና ሌሎች በተለያዩ መልኮች የሚከሰቱ ብዝበዛዎችን ለመቃወም የድርጅቱን አቐም ም ያንጸባርቃል።

የዚህ ዕለት የትኩረት ኣቅጣጫም በመግለጫው መሰረት ዘመናዊ የባርነት ገጽታዎችን ማለትም ህገወጥ የሰዎች ዝውውርን ወሲባዊ ብዝበዛዎችን የህጻናት የጉልበት ብዝበዛን ከፍላጎት ውጪ የሚፈጸሙ ጋብቻዎችን እና ህጻናትን ለጦርነት የሚዳርጉ ሁኔታዎችን ማስወገድ ነው። በየዓመቱም በተለያዩ መፈክሮች ሲታሰብ ቆይቷል። በዚሁ መሰረት የ ተመድ በ 2007 ዕለቱን አትላንቲክ ውቅያኖስን ኣቐጦ ይካሄድ የነበረው የባርያ ንግድ የተወገደበትን 200ኛ ዓመት በማሰብ ማክበሩ የሚታወስ ሲሆን በ 2008 ም እንዲሁ የኣትላንቲክ ማዶው የባሪያ ንግድ ሰለባዎች ማስታወሻ በሚል መሪ ቃል መከበሩ ኣይዘነጋም።

Rola Basamad, Saudi businessman, General Director of Bab Rizq Jameel which empowering the role of women throuh giving them loans. She also a participant in the Qatar International Arab businesswomen Forum 2013; Copyright: privat
ምስል privat

የ ተመድ ዋ/ጸኃፊ ኮፊ ኣናንም የዛሬው ዕለት እኣኣ ማለት ነው ታህሳስ 2 ቀን 2013 በተለያየ መልኩ ድሆችን የተገለሉ የህ/ክፍሎችን ስደተኞችን በተለይም ሴቶችን በማንነታቸው የተጨቆኑ ወገኖችን እና ኣናሳ የህ/ክፍሎችን የሚያጠቃውን ዘመናዊ የባርነት ገጽታን ለማስወገድ ልዩ ትኩረት መስጠታችንን ያመለክታል ሲሉ መልዕክታቸውን ኣስተላልፏል።

በኣሁኑ ጊዜ በዓለማችን 21 ሞሊየን ያህል ሴቶች ወንዶችና ህጻናት በእጃዙር ባርነት ስር ይገኛሉ ያለው ዓ/ዓቀፉ የሰራተኞች ድርጅት ILO በበኩሉ ባርነት ኣሁኑኑ ይቁም በሚል መሪ ቃል ታዋቂ አርቲስቶችን ኣትሌቶችን እና የህግ ባለሙያዎችን ኣሰማርቶ በመንቀሳቀስ ላይ መሆኑን ኣስታውቐል። ይሄው የባርነት ገጽታ ከኢትዮጵያ ኣንጻርም በተለይ በስደተኞችና ሴቶች ላይ ይበልጥ እንደሚንጸባረቅ የገለጹት የILO የ ኢትዮጵያው ጽ/ቤት የቴክኒክ ዋና ኣማካሪ ወ/ሮ ኣይዳ አወልም በቅርቡ ከሳውዲ አረቢያ እየተመለሱ ያሉ ኢትዮጵያውያንን ለዓብነት ያህል ጠቅሷል።

Foreign workers displays his passport as he waits outside a labour office, after missing a deadline to correct his visa status, in Riyadh November 4, 2013. The streets of the Saudi capital Riyadh were unusually quiet on Monday as many expatriates stayed at home to avoid the start of a government crackdown on illegal foreign workers. REUTERS/Faisal Al Nasser (SAUDI ARABIA - Tags: POLITICS BUSINESS EMPLOYMENT SOCIETY IMMIGRATION)
ምስል Reuters/Faisal Al Nasser

በህጋዊ መንገድ የሚሄዱትን ጨምሮ ወደ መካከለኛው ምስራቅ የሚሄዱ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች በተለይም ሴቶች በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የእጃዙር ባርነት ሰለባ ናቸው የሚሉት ወ/ር ኣይዳ በቅርቡ ወደ ኣገር ቤት የተመለሱትን ተመልሰው እንዳይሄዱ ወይንም እሂዚህም ለከፋ ችግር እንዳይዳረጉ ድርጅታቸው ILO የመልሶ ማቐቐም ስራዎችን እያከናወነ መሆኑንም ጠቅሷል።

ጃፈር ዓሊ