የሀይንሪኽ በል ድርጅት ከኢትዮጵያ የመውጣት ውሳኔ
ማክሰኞ፣ ኅዳር 4 2005ማስታወቂያ
በኢትዮጵያ ከሚሰሩት ትልቆቹ መንግሥታዊ ያልሆኑት ድርጅቶች መካከል አንዱ የሆነው ይኸው ድርጅት የኢትዮጵያ መንግሥት ከሦስት ዓመት በፊት ያወጣው የበጎ አድርጎት ተቋማት ሕግ ሀሳብን በነፃ የመግለጽን እና የፖለቲካ ውይይትን የሚገድብ ሆኖ ስላገኘው እዚህ ውሳኔ ላይ መድረሱን በኢትዮጵያ የድርጅቱ ኃላፊ ፓትሪክ ቤርግ ትናንት በበርሊን በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አስረድተዋል። ሕጉ በስድሳ ሀገራት የሚንቀሳቀሰውን የሀይንሪኽ በል ድርጅት ከአካባቢ አጋሮቹ ጋ ዴሞክራሲን ለማስፋፋት፡ የፆታ እኩልነትን ለማራመድ እና ዘላቂ ልማት ለማስገኘት የጀመረውን ስራውን ለመስራት እንዳላስቻለው ቤርግ አክለው ገልጸዋል።
ይልማ ኃይለሚካኤል
አርያም ተክሌ
ነጋሽ መሀመድ