1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የሀይንሪኽ በል ድርጅት ከኢትዮጵያ የመውጣት ውሳኔ

ማክሰኞ፣ ኅዳር 4 2005

መንግሥታዊ ያልሆነው የጀርመናውያኑ የሀይንሪኽ በል ድርጅት ኢትዮጵያን ለቆ እንደሚወጣ እና በአዲስ አበባ የሚገኘውን ጽሕፈት ቤቱንም እስከ ፊታችን ታህሳስ ወር መጨረሻ ድረስ እንደሚዘጋ አስታወቀ።

https://p.dw.com/p/16i8O
Die Heinrich-Böll-Stiftung in Berlin bekommt eine neue Adresse. Die der Partei Bündnis 90/Die Grünen nahestehende Einrichtung zieht in ein eigens errichtetes Gebäude in der Schumannstraße neben Deutschem Theater und Ukrainischer Botschaft in Berlin Mitte. Foto: Tim Brakemeier dpa/lbn +++(c) dpa - Bildfunk+++
በበርሊን የሀይንሪኽ በል ድርጅትዋና ጽሕፈት ቤትምስል picture-alliance/ dpa

በኢትዮጵያ ከሚሰሩት ትልቆቹ መንግሥታዊ ያልሆኑት ድርጅቶች መካከል አንዱ የሆነው ይኸው ድርጅት የኢትዮጵያ መንግሥት ከሦስት ዓመት በፊት ያወጣው የበጎ አድርጎት ተቋማት ሕግ ሀሳብን በነፃ የመግለጽን እና የፖለቲካ ውይይትን የሚገድብ ሆኖ ስላገኘው እዚህ ውሳኔ ላይ መድረሱን በኢትዮጵያ የድርጅቱ ኃላፊ ፓትሪክ ቤርግ ትናንት በበርሊን በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አስረድተዋል። ሕጉ በስድሳ ሀገራት የሚንቀሳቀሰውን የሀይንሪኽ በል ድርጅት ከአካባቢ አጋሮቹ ጋ ዴሞክራሲን ለማስፋፋት፡ የፆታ እኩልነትን ለማራመድ እና ዘላቂ ልማት ለማስገኘት የጀመረውን ስራውን ለመስራት እንዳላስቻለው ቤርግ አክለው ገልጸዋል።

ይልማ ኃይለሚካኤል

አርያም ተክሌ

ነጋሽ መሀመድ