የሁለተኛው ትልቁ ማክሰኞ ምርጫ ውጤት በአሜሪካ
ረቡዕ፣ መጋቢት 7 2008ማስታወቂያ
በመጪው ጥቅምት መጨረሻ ለሚካሄደው የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ የዴሞክራትና የሪፐብሊካን ፓርቲዎችን ወክለው የሚወዳደሩ እጩዎች የመለያ ምርጫ ፉክክሩ ቀጥሏል ። ትናንት በ5 ወሳኝ ፌደራዊ ግዛቶች በተካሄደ ምርጫ ከዴሞክራት ፓርቲ ሂለሪ ክሊንተን ከሪፐብሊካኖች ደግሞ ዶናልድ ትራምፕ ከፍተኛ ውጤት በማስመዝገብ አሸንፈዋል ። ቅዳሜ ሳይጠበቅ በተቀናቃኛቸው በርኒ ሳንደርስ በሚሽጋን የተሸነፉት ሂለሪ ክሊንተን ትናንት በፍሎሪዳ ኦሃዮ ኤሊኖይስና ኖርዝ ካሮላይና ፌደራዊ ግዛቶች አሸንፈዋል። ዶናልድ ትራምፕም በፍሎሪዳ በኖርዝ ካሮላይናና በኤሊኖይስ ድል ቀንቷቸዋል። በኦሃዮ ግን ተሸንፈዋል ። ቆጠራው ባልተጠናቀቀው በሚዙሪ ደግሞ ክሊንተን እየመሩ ነው ። ዝርዝሩን የዋሽንግተን ዲሲው ወኪላችን ናትናኤል ወልዴ ልኮልናል ።
ናትናኤል ወልዴ
ኂሩት መለሰ
ሸዋዬ ለገሠ