1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የሊቢያው መሪ

ረቡዕ፣ የካቲት 23 2003

የሊቢያው ፕሬዚዳንት ሙዓማር ቃዳፊ በሀገር ውስጥም ሆን በውጭ ጫናው እየበረታባቸው እንደሆነ ተገለፀ። ትናንት ከዋና ከተማዋ ትሪፖሊ አቅራቢያ በተቀሰቀሰ ግጭት በርካታ ሰልፈኛ እንደተገደለ ታውቓል። በአንፃሩ የአሜሪካ ጦር ወደ ሊቢያ እየተጠጋ እንደሆነም ተዘግቧል። ማንተጋፍቶት ስለሺ የሊቢያ ወቅታዊ ሁኔታን በተመለከተ የሚከተለውን አጠናቅሯል።

https://p.dw.com/p/R5Hg
ሊቢያ፥ የመንግስት ተቃዋሚያን በቤንጋዚ
ሊቢያ፥ የመንግስት ተቃዋሚያን በቤንጋዚምስል dapd
በሊቢያ የተቀሰቀሰው ሕዝባዊ ዓመፅ ቀጥሎ ትናንት በርካታ ሰው መገደሉ ተዘገበ። ዩናይትድ ስቴትስና ሌሎች የውጭ መንግስታት በሊቢያ ላይ ሊሰነዘር ስለሚችል ወታደራዊ ጥቃት እየመከሩ እንደሆነም ታውቃል። ይህ በእንዲህ እንዳለ፤ ዩናይትድ ስቴትስ የጦር ጀቶቿንና መርከቦቿን ወደ ሊቢያ እያስጠጋች እንደሆነም ተገልጿል። በአንፃሩ የሊቢያ መንግስት ጦር ቱኒዚያን ወደሚያዋስነው የሐገሪቱ ምስራቃዊ ጠረፍ መዝመቱ ተዘግቧል። ማንተጋፍቶት ስለሺ ሂሩት መለሰ