1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የላፍቶ ነዋሪዎች አቤቱታ

ረቡዕ፣ ግንቦት 15 2010

ዘጠኝ ሺሕ አባዎራዎች እንደሚሆኑ የሚናገሩት ነዋሪዎች እንደሚሉት የክፍለ-ከተማዉ ባለሥልጣናት ለተለያዩ አገልግሎቶች ማሟያ በሚል በብዙ ሺሕ የሚቆጠር ገንዘብ ሲቀበሏቸዉ ነበር።

https://p.dw.com/p/2yCVb
Äthiopien Empörung über Abriss von Häusern in Addis Abeba
ምስል DW/H. Go

(Beri.AA) Lafto,AA-Displaced Residents appeal - MP3-Stereo

ከአዲስ አበባ ነፋስ-ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ የሚባለዉ አካባቢ ነዋሪዎች «ቤታችን ፈረሰ፤ መሬታችንንም ተቀማን» በማለት አቤት አሉ።ዘጠኝ ሺሕ አባዎራዎች እንደሚሆኑ የሚናገሩት ነዋሪዎች እንደሚሉት የክፍለ-ከተማዉ ባለሥልጣናት ለተለያዩ አገልግሎቶች ማሟያ በሚል በብዙ ሺሕ የሚቆጠር ገንዘብ ሲቀበሏቸዉ ነበር።በቅርቡ ግን ቤታቸዉን እያፈረሱ ይዞታቸዉን ለሐብታሞች መስጠታቸዉን ነዋሪዎቹ አስታዉቀዋል።የአዲስ አበባዉ ወኪላችን ጌታቸዉ ተድላ ኃይለጊዮርጊስ እንደዘገበዉ «አቤት» ባዮቹ  አዲስ አበባ በሚገኘዉ በተቃዋሚዉ የኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ፅሕፈት ቤት ዉስጥ ተሰብስበዋል።

ጌታቸዉ ተድላ ኃይለጊዮርጊስ

ነጋሽ መሐመድ

ሸዋዬ ለገሰ