የላፍቶ ነዋሪዎች አቤቱታ
ረቡዕ፣ ግንቦት 15 2010ማስታወቂያ
ከአዲስ አበባ ነፋስ-ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ የሚባለዉ አካባቢ ነዋሪዎች «ቤታችን ፈረሰ፤ መሬታችንንም ተቀማን» በማለት አቤት አሉ።ዘጠኝ ሺሕ አባዎራዎች እንደሚሆኑ የሚናገሩት ነዋሪዎች እንደሚሉት የክፍለ-ከተማዉ ባለሥልጣናት ለተለያዩ አገልግሎቶች ማሟያ በሚል በብዙ ሺሕ የሚቆጠር ገንዘብ ሲቀበሏቸዉ ነበር።በቅርቡ ግን ቤታቸዉን እያፈረሱ ይዞታቸዉን ለሐብታሞች መስጠታቸዉን ነዋሪዎቹ አስታዉቀዋል።የአዲስ አበባዉ ወኪላችን ጌታቸዉ ተድላ ኃይለጊዮርጊስ እንደዘገበዉ «አቤት» ባዮቹ አዲስ አበባ በሚገኘዉ በተቃዋሚዉ የኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ፅሕፈት ቤት ዉስጥ ተሰብስበዋል።
ጌታቸዉ ተድላ ኃይለጊዮርጊስ
ነጋሽ መሐመድ
ሸዋዬ ለገሰ