1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የሐዘን መግለጫ ስነ-ስርዓት ለሟች የበረራ ሰራተኞች

ሰኞ፣ መጋቢት 2 2011

የኢትዮጵያ የአውሮፕላን አብራሪዎች ማኅበር ትናንት ቢሾፍቱ አቅራቢያ በተከሰከሰው የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ህይወታቸውን ያጡ ስምንት የበረራ ሰራተኞችን እና 149 ሰዎችን አስበው ውለዋል። በመርሐ- ግብሩ የታደሙ አውሮፕላኑን ያበረው የነበሩት ካፒቴን ያሬድ "ትሁት እና ሰው አክባሪ" እንደነበሩ ተናግረዋል።

https://p.dw.com/p/3EoqH
Äthiopien Trauerfeier für die Opfer des Absturzes der  Boeing 737
ምስል DW/S. Muchie

የሐዘን መግለጫ ስነ-ስርዓት ለሟች የበረራ ሰራተኞች

የኢትዮጵያ አውሮፕላን አብራሪዎች ማህበር አባላት ትናንት ከአዲስ አበባ ወደ ኬንያ ሲበር በተከሰከሰው አውሮፕላን ህይወታቸውን ላጡ ባልደረቦቻቸው እና ተጓዦች ሃዘናቸውን ሲገልጹ ውለዋል፡፡ ሐዘን በተጫነው እና በርካቶች በታደሙበት በዚህ መርሐ ግብር የማህበሩ አባላት የበረራ ሰራተኞችን ሻማ በማብራት አስበዋቸዋል።

በጋራ ለሃዘን የተቀመጡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሰራተኞች ሁሉንም ሟች ባልደረቦቻቸውን እየጠቀሱ፣ ትጋታቸውን እና ስነምግባራቸውን እያስታወሱ፣ ጥቁር ለብሰው፣ በሃዘን እንባ ሲራጩ ውለዋል። አደጋው እጅግ እንዳሳዛናቸው የተናገሩት እነዚህ የስራ ባልደረቦች ህይወታቸውን ያጡት የበረራ ሰራተኞች "ታታሪዎችና ምስጉን ከመሆናቸው የተነሳ መልካም እና ጠንካራዎቹ ተሰባስበው ሄዱብን"  እንዲሉም አድርጓቸዋል፡፡

Äthiopien Trauerfeier für die Opfer des Absturzes der  Boeing 737
ምስል DW/S. Muchie

የማህበሩ ፕሬዝዳንት ካፒቴን የሽዋስ ጌታሁን በተለይ ዋና አብራሪ የነበረው ካፒቴን ያሬድ ጌታቸው የቅርብ ጓደኛቸው እንደነበሩ እና ዘወትር ማክሰኞና ሐሙስ አብረው ኳስ ይጫወቱ እንደነበር ለDW ተናግረዋል፡፡ አስደንጋጩ አደጋ ባይከሰት ለሀዘን ሳይሆን እንደወትሮው ለኳስ ነበር የምንገናኘው ብለዋል።  

በሀዘን መግለጫ ስነ ስርዓቱ ላይ የታደመውን የአዲስ አበባው ዘጋቢያችን ሰለሞን ሙጬን ዘገባ ለማድመጥ የድምጽ ማዕቀፉን ይጫኑ።  

ሰለሞን ሙጬ 

ተስፋለም ወልደየስ 

እሸቴ በቀለ