የሕገ ወጥ የጫት ነጋዴዎች ክስ በዩኤስ አሜሪካ
ሐሙስ፣ ሚያዝያ 11 2004ማስታወቂያ
ተከሳሾቹ ባለፉት ስድስት ዓመታት ብዙ ሚልዮን የሚቆጠር ዶላር ያስገኘ ጫት ማዛዋወራቸውን የክሱ መዝገብ አመልክቶዋል። የህግ ባለሞያና ጠበቃዉ ዶክተር ፍፁም አቻሜለህ ፊደራሉ ህግ ላይ በወንጀልነት የተጠቀሰዉ ይላሉ « በፊደራሉ ህግ የተፃፈዉ ጫት ዉስጥ ስላሉ ንጥረ ነገሮች ነዉ። አንደኛዉ ካቲኖን የተባለ ንጥረ ነገር ሲሆን ፣ ሁለተኛዉ ደግሞ ካቲን የተባለ ንጥረ ነገር ነዉ ያለዉ ጫት። ካቲኖን የሚገኘዉ ጫት ከተቆረጠ 48 ሰዓት ያልሞላዉ እርጥብ ጫት ዉስጥ ነዉ። በአሜሪካ ዉስጥ እርጥብ ጫት ይዞ መገኘት ከአንድ ዓመት በላይ የሚያስቀጣ ከባድ ወንጀል ነዉ።»
አበበ ፈለቀ
አርያም ትክሌ
ነጋሽ መሀመድ