የመረጃ ቴክኖሎጂ አጠባበቅ
ረቡዕ፣ መጋቢት 3 2006ማስታወቂያ
በመረጃ አጠባበቅ ላይ የሚታየው አሰራር፣ በተለይ፣ አሜሪካዊው ኤድዋርድ ስኖውደን ያጋለጠው የዩኤስ አሜሪካ ብሔራዊው ፀጥታ ድርጅት ፣ በምሕፃሩ «ኤን ኤስ ኤ» ግለሰቦችን ፣ ያገር መሪዎችን ጭምር በሰለለበት ተግባር ሰበብ ተዓማኒነት እያጣ ሄዶዋል። ይህን ተከትሎ የመረጃ አጠባበቅ በዘመናዊ ዘዴ ተሻሽሎ ሊቀርብ እንደሚገባ ትርዒቱን ከብሪታንያዊው አቻቸው ዴቪድ ካምረን ጋ ባንድነት የከፈቱት የጀርመን መራሒተ መንግሥት አንጌላ ሜርክል አሳስበዋል።
ሄንሪክ በመ/ይልማ ኃይለ ሚካኤል
ተክሌ የኋላ