1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የመቀሌ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች

ዓርብ፣ ሰኔ 25 2013

ከማክሰኞ ጀምሮ የስልክ እና ኢንተርኔት ግንኙነት የተቋረጠ ቢሆንም መቀሌ የሚገኘው ዘጋቢያችን ሚሊየን ኃይለ ሥላሴ ባገኘው የኢንተርኔት መስመር ተጠቅሞ ጥቂት የመቀሌ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ያሉበትን ሁኔታ እንዲገልጹለት ጠይቆ ድምጻቸውን ልኮልናል።

https://p.dw.com/p/3vx3s
Äthiopien Stadtansicht Mekele
ምስል DW/M. Hailessilasie

«ያሉበትን ሁኔታ ይናገራሉ»

የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት መቀሌን ለቅቆ መውጣቱ ከተሰማ ወዲህ በትግራይ ክልል የተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ልጆቻቸው የሚማሩ ወላጆች መገናኛ ስልቶች ባለመኖራቸው ዕጣ ፈንታቸው ስጋት ላይ እንደጣላቸው ይናገራሉ። ለዶቼ ቬለ በኢሜይልና በተለያዩ የማኅበራዊ መገናኛ መስመሮች እባካችሁ ስጋታችንን አሰሙልን፤ ሁኔታውንም አጣሩልን የሚሉ መልእክቶችም ይልካሉ። ከማክሰኞ ጀምሮ የስልክ እና ኢንተርኔት ግንኙነት የተቋረጠ ቢሆንም መቀሌ የሚገኘው ዘጋቢያችን ሚሊየን ኃይለ ሥላሴ ባገኘው የኢንተርኔት መስመር ተጠቅሞ ጥቂት የመቀሌ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ያሉበትን ሁኔታ እንዲገልጹለት ጠይቆ ድምጻቸውን ልኮልናል።

ሸዋዬ ለገሠ

ነጋሽ መሐመድ