የመድሐኒት አጠቃቀም በኢትዮጵያ-ዉይይት
እሑድ፣ ነሐሴ 18 2006ማስታወቂያ
በዘፈቀደ የሚሸመቱ፤ የተመረቱበት ሐገር፤ጊዜ እና አጠቃቀማቸዉ በግልፅ የማይታወቁ መድሐኒቶችን መዉሰድ ሐኪሞች እንደሚሉት፤ ሲያንስ የአካል-ሲበዛ የሕይወት ዋጋ ያስከፍላሉ።ኢትዮጵያ ዉስጥ ግን አደጋ የሚያስከትሉ መድሐኒቶች ሳይቀሩ በየመድሐኒት መደብሩ እንደልብ መሸጣቸዉ በሠፊዉ እየተነገረ ነዉ።በተለይ አስቸኳይ የፅንስ መከላከያ እንክብል (Emergency Ccontraceptive pill)ን ካንድ ጊዜ በላይ ከሐኪም ትዕዛዝ ዉጪ መዉሰድ በተጠቃሚዎቹ ላይ ከፍተኛ ጉዳት እንደሚያስከትል ባለሙያዎች እየመከሩ ነዉ።መድሐኒቱን ግን ማንም ከመድሐኒት መደብር መግዛት ይችላል። የዉይይት ዝግጅታችን የመድሐኒቱ እቅርቦት፤ ሽያጭ፤ አጠቃቀሙንና ጥንቃቄዉን ይቃኛል።
ነጋሽ መሐመድ
ልደት አበበ