1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የሙስሊሞች ተቃዉሞና ሰብዓዊ መብት በኢትዮጵያ

ሐሙስ፣ ሐምሌ 19 2004

ወራት ያስቆጠረዉ የኢትዮጵያ ሙስሊም ምዕመናን አቤቱታና ሰላማዊ ተቃዉሞ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ደረጃዉ ከፍ እያለ መሄዱ እየተዘገበ ነዉ። ባለፈዉ ሳምንት ማለቂያ ቅዳሜ የመንግስት ፀጥታ ኃይሎች መንግስት በሃይማኖታችን ጣይቃ ገብቷል ካሉ ሙስሊም

https://p.dw.com/p/15ef5
***ACHTUNG: Das Foto darf nur für die Rubrik "Der Blick aus meinem Fenster" verwendet werden*** Thema: Der Blick aus meinem Fenster: Addis Abeba, Äthiopien Foto: Solomon Mengist .
ምስል Solomon Mengist

 አማንያን ጋ መጋጨቱ ሮይተርስ ዘግቧል።  በተፈጠረዉ መፋጠጥም ቤተዕምነታቸዉ ዉስጥ የፀጥታ ኃይሎች ገብተዉ አንዳንዶችን ሲያስሩ፤ በትር የደረሰባቸዉ እንዳሉም ተነግሯል። ዓለም ዓቀፉ የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋች HRW ሁኔታዉን በጥሞታ እየተከታተለ እንደሚገን በመግለፅ፤ ለተባባሰዉ ሁኔታ መንስኤዉ የሀገሪቱ ህገ መንግስት አለመከበር እንደሆነ አመልክቷል። የድርጅቱን የአፍሪቃ ተመራማሪ ያነጋገረችዉ ሸዋዬ ለገሠ ዘገባ አጠናቅራለች።

ሸዋዬ ለገሠ

አርያም ተክሌ