1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የሙከራ ኤሌክትሪክ ሽያጭ ለጅቡቲ

ረቡዕ፣ ሰኔ 8 2003

ኢትዮጵያ ወደ ውጭ ለመሸጥ ካቀደችው የኤሌክትሪክ ኃይል ለጅቡቲ የመጀመሪያ የሙከራ ሽያጭ ጀመረች ።

https://p.dw.com/p/RTmc
ምስል picture alliance/dpa

የኢትዮጵያ መብራት ኃይል ኮርፖሬሽን የህዝብ ግንኙነት ቡድን መሪ አቶ አዲስ ታገለ ዛሬ ለዶቼቬለ እንደተናገሩት ካለፈው ወር አንስቶ የሙከራው የኤሌክትሪክ ሽያጭ ተጀምራል ። ኮርፖሬሽኑ አሁን ለጅቡቲ የሚልከው ኃይል ሃያ ሜጋዋት መሆኑን አቶ አዲስ አስታውቀዋል ። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት እያደገ የመጣውን የሐገሪቱን ፍጆታ ማርካት አልቻለም ። በተደጋጋሚ የኤሌክትሪክ ኃይል መቋረጥ ያጋጥማል ። ባላፈው ሠኞ የዩናይትድ ስቴትስ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሂለሪ ክሊንተን በአፍሪቃ ህብረት አዳራሽ ንግግር ሲያደርጉ እንኳን አዲስ አበባ ውስጥ መብራት ተቋርጦ ነበር ። በዚህ መሐል ነው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን የኤሌክትሪክ ኃይል ወደ ውጭ መላክ የጀመረው ።

ታደሰ እንግዳው

ሂሩት መለሰ

አርያም ተክሌ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ