1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የማዕከላዊ  ጎንደር ዞን ተፈናቃዮች

ረቡዕ፣ ሚያዝያ 30 2011

ክልሉ እንዳስታወቀው እስካሁን ወደ ቀያቸው የተመለሱት ቁጥር ከ13 ሺህ በላይ ነው። በምዕራብና ማዕከላዊ ጎንደር ዞኖች በአማራና በቅማንት ማኅበረሰብ መካከል በዚህ ዓመት በተፈጠረው ግጭት ለተፈናቀሉት ሰዎች የመኖሪያ ቤቶች እየተገነቡ መሆኑንም የክልሉ የምግብ ዋስትና መርሃ ግብር ማስተባበሪያ ኮሚሽን አስታውቋል።

https://p.dw.com/p/3I8lx
Äthiopien Bahr Dar - Eyasu Msfin PR Direktor der Disaster prevention Agency PC
ምስል DW/A. Mekonnen

ለተፈናቀሉት የመኖሪያ ቤቶች እየተገነቡ ነው።

ከአማራ ክልል ማዕከላዊ ጎንደር ዞን የተፈናቀሉ ሰዎች ወደቀያቸው እየተመለሱ መሆኑን የአማራ ክልል መንግስትና የየአካባቢው ነዋሪዎች ተናገሩ፡፡ክልሉ እንዳስታወቀው እስካሁን ወደ ቀያቸው የተመለሱት ቁጥር ከ13 ሺህ በላይ ነው። በምዕራብና ማዕከላዊ ጎንደር ዞኖች በአማራና በቅማንት ማህበረሰብ መካከል በዚህ ዓመት በተፈጠረው ግጭት ለተፈናቀሉት ሰዎች የመኖሪያ ቤቶች እየተገነቡ መሆኑንም የክልሉ የምግብ ዋስትና መርሃ ግብር ማስተባበሪያ ኮሚሽን አስታውቋል። በግጭቱ በሁለቱም ዞኖች ህይወት ጠፍቷል፣ ከ6000 በላይ ቤቶች ተቃጥለዋል፡፡ ዓለምነው መኮንን ከባሕር ዳር ዝርዝር ዘገባ አለው።
ዓለምነው መኮንን
ኂሩት መለሰ
ነጋሽ መሐመድ