1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የምሥራቅ ኮንጎ ውጊያ ማብቃት

ረቡዕ፣ ጥቅምት 27 2006

የዴሞክራቲክ ኮንጎ ሬፓብሊክ መንግሥት እና አማፅያኑ «ኤም 23» ቡድን በምሥራቃዊ የሀገሪቱ አካባቢ የሚያካሂዱትን ውጊያ ለማብቃት በካምፓላ ዩጋንዳ ከብዙ ወራት ወዲህ የጀመሩት ድርድር ካለውጤት በተበተነበት ባሁኑ ጊዜ የኮንጎ ጦር በአማፅያኑ ላይ ሙሉ ድል ተቀዳጅቶዋል።

https://p.dw.com/p/1AD9n
GettyImages 179483815 Democratic Republic of Congo (FARDC) soldiers celebrate near Kibati, near Goma on September 4, 2013. M23 army mutineers, whose 16-month rebellion had seen them occupying Kibati for over a year, have retreated from their positions in the hills around Goma in the face of an offensive by the military and a new United Nations combat force. AFP PHOTO / CARL DE SOUZA (Photo credit should read CARL DE SOUZA/AFP/Getty Images)
ምስል Carl de Souza/AFP/Getty Images

ጦሩ « ኤም 23 » በሰሜን ኪቩ ግዛት ይዟቸው የነበሩትን የመጨረሻ ሰፈሮች ባለፈው ሰኞ ሌሊት መልሶ ተቆጣጥሮዋል። ይህን ተከተሎም አማፅያኑ መሸነፋቸውን እና 18 ወራት የዘለቀውን ውጊያ ማብቃታቸውን በማረጋገጥ፣ የጦር መሣሪያ ትጥቃቸውን ለመፍታት እና ለውዝግቡም የፖለቲካ መፍትሔ ለማፈላለግ ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል።
ከኮንጎ ጦር ያመፁ የቱትሲ ጎሣ አባላት ያቋቋሙት እና በምሥራቃዊ ኮንጎ የሚንቀሳቀሰው «ኤም 23» የተባለው ቡድን እርግጥ በወቅቱ እጅግ ተዳክሞዋል። ይሁንና፣ ቡድኑ አንድ ሚልዮን ሕዝብ የሚኖርባትን የምሥራቅ ኮንጎ ከተማ፣ ጎማን እአአ ኅዳር፣ 2012 ዓም ለአጭር ጊዜ ተቆጣጥሮ እንደነበር ይታወሳል። የኮንጎ ጦር በሀገሩ ከተሰማራው የተመድ ሰላም አስከባሪ ጓድ፣ ሞንዩስኮ ድጋፍ በማግኘት ከጥቂት ሳምንታት በፊት በ « ኤም 23 » ላይ ባካሄደው ጠንካራ የጥቃት ዘመቻ ሩንዮኒን እና ቻንዙን ከዓማፅያኑ ማስለቀቅ መቻሉን የጦሩ ቃል አቀባይ ኦሊቭየ ሀሙሊ አስታውቀው፣ ጦሩ ባካባቢው በሚንቀሳቀሱ ሌሎች ቡድኖች ዘመቻውን እንደሚቀጥል አስረድተዋል።
« ቀጣዩ ርምጃ ማይ ማይንን እና የ« ኤፍ ዲ ኤል አር »ን የመሳሰሉ የኮንጎ እና ሌሎች የውጭ ሀገር ታጣቂ ቡድኖችን ትጥቅ ማስፈታት ይሆናል። ቡድኖቹ ትጥቃቸውን መፍታት ካልፈለጉ ልክ በ « ኤም 23 » ላይ ባካሄድነው ዓይነት ዘመቻ እናስፈታቸዋለን። »
ባለፉት ጊዚያት የተመድ በተደጋጋሚ ከርዋንዳ የጦር እና የገንዘብ ርዳታ ያገኛል ያለው «ኤም 23» እአአ ለ1994 ዓም የርዋንዳ ጎሳ ጭፍጨፋ ተጠያቂ የሆኑት ሁሉ ሚሊሺያዎች ካቋቋሙት የርዋንዳ ነፃነት ዴሞክራሲያዊ ኃይላት፣ የ« ኤፍ ዲ ኤል አር » ሁቱ ዓማፅያንም ጋ ውጊያ ሲያካሂድ ቆይቷል። የኮንጎ መንግሥት አሁን በ« ኤፍ ዲ ኤል አር » አንፃር ርምጃ ለመውሰድ መወሰኑን የ «ኤም 23» ዓማፅያን እንደ ጥሩ ክስተት ሊመለከቱት ይችላሉ።
የኮንጎ ጦር አሁን ወታደራዊ ድል ማስመዝገቡ እና « ኤም 23 »ም ሽንፈቱን አምኖ መቀበሉ ብቻውን ግን አካባቢውን ማረጋጋቱን ብዙዎች ተጠራጥረውታል። ምንም እንኳን ሁለቱ ተቀናቃኝ ወገኖች 18 ወራት የዘለቀው ውጊያ እንዲያበቃ ካለፉት አንድ ዓመት ገደማ ወዲህ በካምፓላ ዩጋንዳ ቢደራደሩ እና እስካሁንም ይህ ነው የሚባል አሰተማማኝ የፖለቲካ መፍትሔ ላይ ባይደርሱም፣ በዚህ ሳምንት መጨረሻ አንድ የሰላም ውል ይፈራረማሉ ተብሎ ይጠበቃል። እርግጥ፣ በድርድሩ ወቅት የኮንጎ መንግሥት ለ «ኤም 23 » ከገባው ቃል መካከል ለዓማፅያኑ ምሕረት ማድረግ የተሰኘው ይገኝበታል። መንግሥት የገባውን ቃል ካላከበረ በምሥራቃዊ ኮንጎ ዘላቂ ሰላም እንደማይወርድ ዩጋንዳዊው የምጣኔ ሀብት ምሁር እና ጋዜጠኛ አሊ ሙታሳ አስጠንቅቀዋል።
« እንደ « ኤም 23 » ተደራዳሪዎች ዘላቂ ሰላም የሚወርደው በካምፓላው ውይይት ላይ የተደረሱት ስምምምነቶች ሙሉ በሙሉ በተግባር ከተተረጎሙ ብቻ ነው። እና መንግሥት ስምምነቶቹን በተግባር ላለመተርጎም ከወሰነ፣ ይህ ለ«ኤም 23» ዓማፅያን የጦር መሣሪያቸውን እንደገና ለማንሳት እና ውጊያውን ለመቀጠል ምክንያት ይፈጥርላቸዋል።»
እንደ አሊ ሙታሳ ግምት፣ የኮንጎ መንግሥት ጦሩ አሁን ባስመዘገበው ወታደራዊ ርምጃ በመተማመን ስምምነቶቹን ሊያፈርስ ይችላል። የኮንጎ መንግሥት ወደ ካምፓላው ድርድር ጠረጴዛ እንደሚመለስ፣ ግን የድርድሩ አቅጣጫ እንደሚቀየር የመንግሥቱ ቃል አቀባይ ላምቤር ሜንዴ ትናንት ምሽት የሰጡት መግለጫ፣ የሁኔታውን አደገኛነት የሚጠቁም ነው፣ ምንም እንኳን ውጊያው አሁን ቢያበቃም።
በኮንጎ የተመድ ሰላም አስከባሪ ጓድ ተልዕኮ፣ የሞንዩስኮ መሪ ማርቲን ኮብለር ባካባቢው የሚንቀሳቀሱ ታጣቂ ቡድኖች በጠቅላላ፣ «ኤፍ ዲ ኤል አር» ጭምር፣ ገና አስተማማኝ ያልሆነውን የፀጥታ ሁኔታ ምክንያት በማድረግ ወደ ኃይሉ ተግባር እንዳይገቡ ጥሪ አቅርበዋል። ይህን ካደረጉ ግን ሞኑስኮ በአንፃራቸው ርምጃ እንደሚወስድ አስታውቀዋል።
የተመድ የስደተኞች ጉዳይ ተመልካች መሥሪያ ቤት ባልደረባ ወይዘሮ ሉሲ ቤክ እንዳመለከቱት፣ በብዙ መቶ ሺህ የሚቆጠር የምሥራቅ ኮንጎ ሕዝብ በ«ኤም 23» እና በመንግሥቱ ጦር መካከል ባለፉት በርካታ ወራት በቀጠለው ከባድ ውጊያ አካባቢውን እየለቀቀ ሸሽቶዋል። ውጊያው እአአ በ2012 ዓም የመፀው ወራት ከተጀመረ ወዲህ 800,000 ሰው ሲሸሽ፣ ባለፉት ሁለት ሳምንታት ውጊያ ብቻ 19,000 ወደ ጎረቤት ዩጋንዳ ተሰዶዋል።
«ብዙ ሰዎች ከባድ የቦምብ ድብደባ መካሄዱን ገልጸውልናል፣ እኛም የቆሰሉ ሰዎች አይተናል። ብዙዎችም የሞቱ ሰዎች እንዳዩ፣ አንዳንድ የሚያውቋቸው ሰዎች አስከሬን መመልከታቸውን ነግረውናል። አንድ ያነጋገርኩት ሰውየ ድንበር ተሻግረው ሲሸሱ የተገደሉ አምስት ወይም ስድስት የሚያውቃቸው ሰዎች ማየቱን ገልጾልኛል።»
ስደተኞቹ አሁን ከ «ኤም 23 » ድል መሆን በኋላ እፎይ ማለት መቻል አለመቻላቸው የኮንጎ መንግስት እና «ኤም 23 » ዘላቂ የፖለቲካ መፍትሔ በሚያገኙበት ሁኔታ ላይ ጥገኛ ይሆናል።

Refugees queue to receive material from the UNHCR (jerrycans, mosquitoe nets, plastic sheets, covers, cooking materials) on March 5, 2013, at Rwamwanja refugee camp, in the Kamwenge district, western Uganda, home to over 35000 refugees, most of them from Democratic Republic of Congo. Four thousand people fled new clashes in eastern Democratic Republic of Congo on February 28, 2013 and crossed the border into neighbouring Uganda, the Red Cross said on March 1. '4,000 refugees crossed into Uganda through Bunagana border,' the Red Cross said. AFP PHOTO / MICHELE SIBILONI (Photo credit should read MICHELE SIBILONI/AFP/Getty Images)
ምስል Michele Sibiloni/AFP/Getty Images
GettyImages 178265177 The head of the UN Stabilization Mission in the Democratic Republic of Congo (MONUSCO) and special envoy of the UN secretary-general, Martin Kobler (R), gives a press conference on August 28, 2013 at the headquarters of the UN peacekeeping mission in Kinshasa. UN attack helicopters joined Congolese government troops in an operation on August 28 against rebels in the east of the Democratic Republic of Congo, the UN peacekeeping force said. The operation against M23 rebels in the hills of Kibati north of the regional capital Goma also involved UN and DR Congo army artillery. AFP PHOTO / JUNIOR D. KANNAH (Photo credit should read JUNIOR D.KANNAH/AFP/Getty Images)
ምስል Junior D.KannahAFP/Getty Images)
M23 rebellion Major John (L) and Colonel Bildunterschrift: M23 rebellion Major John (L) and Colonel Vianney Kazarama walk as they explain that the M23 does not support Bosco Ntaganda, the chief of staff of another regional militia the National Congress for the Defense of the People, at the Kavumu hill in rebel-held territory in North Kivu, eastern Democratic Republic of the Congo (DRC), on June 3, 2012. An AFP correspondent in Congo and an independent French journalist were briefly detained on June 3 by M23 forces in the Virunga region and then interrogated by civil intelligence officers before being released. Fighting between M23 rebels and Congolese soldiers resumed on June 4 in the Virunga park where the rebel movement embroiled in cat-and-mouse clashes with loyalist troops for weeks has been holding its position on the hills of Runyonyi. AFP PHOTO / MELANIE GOUBY (Photo credit should read Melanie Gouby/AFP/GettyImages) Erstellt am: 05 Jun 2012
ምስል Melanie Gouby/AFP/GettyImages

ፊሊፕ ዛንድነር/አርያም ተክሌ

ሸዋዬ ለገሠ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ