1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የሠራተኞች  አድማ በኮይሻ ኃይል ማመንጫ

ዓርብ፣ ሚያዝያ 11 2011

ከአምስት  ሺህ በላይ የሚሆኑ  የኮይሻ ሃይል ማመንጫ ግድብ ሠራተኞች  የሥራ ማቆም አድማ ከመቱ አንድ ሳምንት ሆናቸው።  በግድቡ ፕሮጀክት የሥራ ኃላፊዎች  ተፈድሞብናል  የሚሉት  የአስተዳደር በደል ፣ ሙስና እና  የመብት ጥሰቶች  የአድማው  መነሾ  ምክንያት  ናችው  ተብሏል።

https://p.dw.com/p/3H5yV
Äthiopien | streikende Arbeiter des Koysha Hydroelectric Kraftwerks
ምስል DW/S. Wegayehu

«የፕሮጀክቱ አመራሮች ከሠራተኞች ጋር ድርድር በማድረግ ላይ ናቸው»

  ከአካባቢው የሚውጡ  መረጃዎች  እንሚያመለቱት  በአሁኑ ወቅት   ማቆም  አድማው  ምክንያት ይል ማመንጫ  ግድብ  ግንባታ  ሙሉ  በሙሉ  እንደተቋረጠ  ይገኛል። ከአካባቢው የሚውጡ መረጃዎች እንዳሚያመለከቱት በሥራ ማቆም አድማው ምክንያት የኃይል ማመንጫ ግድብ ግንባታው አሁንም ሙሉ በሙሉ እንደተቋረጠ ይገኛል። በአሁኑ ውቅትም  የፕሮጀክቱ አመራሮች ከሠራተኞቹ ጋር ድርድር  በማካሄድ ላይ እንደሚገኙም ለማወቅ ተችሏል።

Äthiopien | streikende Arbeiter des Koysha Hydroelectric Kraftwerks
ምስል DW/S. Wegayehu

ዘግይቶ  በደረሰን  ዜና ደግሞ  ሠራተኞቹ  ዛሬ ሲያደረጉት የነበረውን ድርድር  አሁን ማምሻወን በማጠናቀቅ ከነገ  ቅዳሜ ጀምሮ  ወደሥስራ  ገበታቸው ለመመለስ  ከስምምነት ላይ ደርሰዋል። ሠራተኞቹ ከስምምነት ላይ ሊደርሱ የቻሉት የአስተዳደር በደል ፈድመዋል በሚል ቅሬታ ሲነሳባቸው ከነበሩት   የፕሮጅክቱ  የሥራ ሃላፊዎች  መካከል ሁለቱ ከሥራቸው በመታገዳቸው መሆኑም ተሰምቷል። የዲ ደብሊው ታማኝ ምንጮች እንዳረጋገጡት እገዳ የተጣለባቸው ሁለቱ ሃላፊዎች የግድቡን ግንባታ በኮንትራት እያከናወነ  በሚገኘውና  ሳሊኒ በተባለው ኩባንያ ወስጥ በከፍተኛ  የሰው ሀብትና የፋይናንስ  ኃላፊነት ቦታዎች በማገልገል የነበሩ መሆናችው ታውቋል።  

ሸዋንግዛው ወጋየሁ

ሸዋዬ ለገሠ

ማንተጋፍቶት ስለሺ