1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የርዕዮት ክስና የጠበቃዋ ተቃዉሞ

ረቡዕ፣ ጥር 1 2005

ርዕዮት ዓለሙ ከዚሕ ቀደም የበታች ፍርድ ቤት አስራ-አራት ዓመት እስራትና የገንዘብ መቀጮ በይኖባት ነበር።ይግማኝ ሰሚ ፍርድ ቤት ግን ቅጣቱን ወደ አምስት-ዓመታት እስራት ዝቅ አድርጎታል።ርዕዮት ዓለሙ ለሰበር ሰሚዉ ችሎት አቤት ያለችዉ የአምስት ዓመቱ እስራትም የሕግ አተረጓገም ክፍተት አለበት በሚል ነበር

https://p.dw.com/p/17Gol
Pedestrians walk past the Federal High Court building in Addis Ababa, Ethiopia Tuesday, Nov. 1, 2011. A witness in a terror trial against two Swedish journalists Johan Persson and Martin Schibbye arrested during a clash with rebels in the Ogaden in the country's restive east in July told the court on Tuesday that the pair planned to "support" a rebel group. The two Swedes pleaded not guilty to charges of terrorism during a preliminary hearing Oct. 20 but admitted to having violated immigration laws. (AP Photo)
ምስል AP

የጋዜጣ አምደኛ ርዕዮት ዓለሙ በአሸባሪነት ወንጀል የተበየነባት ቅጣት እንዲሠረዝ ለኢትዮጵያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሠበር ሰሚ ችሎት ያቀረበችዉን አቤቱታ ችሎቱ ዉቅድቅ አደረገዉ።ርዕዮት ዓለሙ ከዚሕ ቀደም የበታች ፍርድ ቤት አስራ-አራት ዓመት እስራትና የገንዘብ መቀጮ በይኖባት ነበር።ይግማኝ ሰሚ ፍርድ ቤት ግን ቅጣቱን ወደ አምስት-ዓመታት እስራት ዝቅ አድርጎታል።ርዕዮት ዓለሙ ለሰበር ሰሚዉ ችሎት አቤት ያለችዉ የአምስት ዓመቱ እስራትም የሕግ አተረጓገም ክፍተት አለበት በሚል ነበር።ትናንት አዲስ አበባ ያስቻለዉ ሰበር ሰሚ ፍርድ ቤት ግን አቤቱታን ዉድቅ አድርጎታል።የርዕዮት ጠበቃ የችሎቱን ዉሳኔ አልተቀበለቱም።ዩሐንስ ገብረ እግዚ አብሔር ዝር ዝር ዘገባ ልኮልናል።

ዩሐንስ ገብረ እግዚ አብሔር

ነጋሽ መሐመድ

አርያም ተክሌ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ