የሰማያዊ ፓርቲ ሮሮና የምርጫ ቦርድ መልስ
ረቡዕ፣ መጋቢት 30 2007ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ መንግሥት ተቃዋሚ የፖለቲካ ማሕበር ሰማያዊ ፓርቲ ምርጫ ቦርድ ያገዳቸው 15 ተወዳዳሪዎቹ በፍርድ ቤት ትዕዛዝ በአማራ ክልል በዕጩነት እንዲመለሱ ውሳኔ ቢሰጥም የእጩነት መታወቂያ ተነፍጓቸዋል ሲል አማረረ ።ፓርቲው እንዳስታወቀው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የፍርድ ቤት ትዕዛዝ ባለማክበር ለእጩዎቹ መታወቂያ አልሰጠም ። ምርጫ ቦርድ ከዚህ ቀደም በነዚህ እጩዎች ላይ የተለያዩ ምክንያቶችን በማቅረብ ከእጩነት ቢያገላቸውም ጉዳዩን ወደ ፍርድ ቤት ወስዶ እንዲወዳደሩ እንደተበየነለት ፓርቲው አስታውቋል ።የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በበኩሉ ፍርድ ቤት እገዳው እንዲነሳላቸው ውሳኔ የሰጠው ለ3 የሰማያዊ ፓርቲ አባላት እንደሆነና ይህንኑም ተግባራዊ ማድረጉን አስታውቋል ።ዝርዝሩን የአዲስ አበባው ወኪላችን ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር ልኮልናል ።
ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሄር
ኂሩት መለሰ
ነጋሽ መሀመድ