1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የሰሜን ሱዳን ደቡባዊ ግዛት ግጭትና ርዳታ

ረቡዕ፣ ጥቅምት 21 2005

ደቡብ ሱዳን ካደችም፥ አመነች የደቡባዊ ኮርዶፋን ዉጊያ አሁንም እንደቀጠለ ነዉ።የመንግሥት ጦር አማፂያኑ ወደሚቆጣጠሩት አካባቢ ርዳታም ሆነ ሌላ ቁሳቁስ እንዳይደርስ በየስፍራዉ ኬላ አቁሞ እየተቆጣጠረ ነዉ።

https://p.dw.com/p/16aFT
Karte Sudan mit Südsudan und Darfur

የሰሜን ሱዳን መንግሥት ደቡባዊ ኮርዶፋን ግዛት ከቤት ንብረቱ የተፈናቀለዉን ሕዝብ ርዳታ ሰጪዎች እንዲረዱት ይፈቅድ ዘንድ የተባበሩት መንግሥታት፥ የአረብ ሊግና የአፍሪቃ ሕብረት ግፊት እንዲያደርጉበት ግብረ-ሠናይ ድርጅቶች ጠየቁ።የሰሜን ሱዳን መንግሥት ጦርና አማፂያን ደቡብ ኮርዶፋን ዉስጥ የገጠሙት ዉጊያ ከ160 ሺሕ በላይ ሕዝብ አፈናቅሏል።ለጋሽ ድርጅቶች እንደሚሉት ተፈናቃዩ ሕዝብ ምግብ፥ መድሐኒት መጠለያ አያገኝም።


የሰሜን ሱዳን መንግሥት ከደቡብ ኮርዶፋን አማፂያን ጋር የገጠመዉ ጦርነት የሌላ፥ ሰብአዊ ድቀት ሰበብ ከሆነ አምና ሐምሌ ዓመት ደፈነ።ጦርነቱን የሸሹ በብዙ ሺሕ የሚቆጠሩ ስደተኞች የኢትዮጵያ ሠፍረዋል።የዓለም ምግብ ድርጅት (WFP) እና የሌሎች እርዳታ ሰጪ ተቋማት ባለሥልጣናት እንደሚሉት ኢትዮጵያ የሰፈሩትን ስደተኞች መርዳቱ ብዙም አላሰቸገራቸዉም።

እዚያዉ ኮርዶፋን፥ የሱዳን አብዮታዊ ግንባር የተሰኘዉ አማፂ ቡድን በሚቆጣጠረዉ አካባቢ ለሠፈረዉ ተፈናቃይ እርዳታ ለማቀበል ግን የዓለም ምግብ ድርጅት ቃል አቀባይ ቻሊስ ማክዶናሕ እንደሚሉት እስካሁን ከካርቱም መንግሥት ፍቃድ አላገኙም።
            
«አማፂያኑ በሚቆጣጠሩት አካባቢ ሁኔታዉ የተወሳሰበ ነዉ።ወደ አካባቢዉ ለመግባት ገና እየተደራደርን ነዉ።WFP ሱዳን ዉስጥ ብዙ ሰዎችን ይረዳል።ዳርፉር፥ ማዕከላዊና ምሥራቃዊ ሱዳን አራት-ነጥብ-ሁለት ሚሊዮን ሕዝብ ለመርዳት እየጣርን ነዉ።የደቡባዊ ኮርዶፋን ሕዝብም ርዳታ በጣም ያስፈልገዋል።በነዚሕ አካባቢዎች በተቻለ ፍጥነት ርዳታ ማቀበል እንድንችል አበክረን እየጣርን ነዉ።»

ለወትሮዉ ምንም ወይም ትንሽ የሚታወቀዉ የሱዳን አብዮታዊ ግንባር ሐቻምና ሐምሌ ካዱግሊ ከተሰኘችዉ የደቡባዊ ኮርዶፋን ርዕሠ-ከተማ አጠገብ የሚገኙ አካባቢዎችን ከተቆጣጠረ ወዲሕ ግዛቲቱ ሠላም አታዉቅም።የሰሜን ሱዳን መንግሥት ቡድኑን ያደራጀችና የምትረዳዉ ደቡብ ሱዳን ናት በማለት ይወነጅላል።የደቡብ ሱዳኑ ፕሬዝዳት ሳልቫ ኪየር ግን ዉንጀላዉን አይቀበሉትም።ይሁንና  ያሁኑ የኮርዶፋን አማፂ ቡድን አባላት የደቡብ ሱዳን ነፃ አዉጪ ጦር (SPLA/M) አካል ሆነዉ የሱዳንን መንግሥት ይወጉ እንደነበር ኪየር አልካዱም።
            
«እነዚሕ ሰዎች የSPLA/M አካል ሆነዉ አብረዉን የተዋጉ ቢሆንም ባሁኑ ዉጊያ እኛ አልተሳተፍንም።በካርቱም መንግሥትና በደቡባዊ ኮርዶፋን ሕዝብ መካካል በሚደረገዉ ዉጊያ አንሳተፍም።»

ደቡብ ሱዳን ካደችም፥ አመነች የደቡባዊ ኮርዶፋን ዉጊያ አሁንም እንደቀጠለ ነዉ።ባለፈዉ እሁድ  የካርቱም መንግሥት አየር ሐይል ጣለዉ በተባለ ቦምብ አንድ ሕፃን ሲገደል፥ ሌሎች አራት ቆስለዋል።የመንግሥት ጦር አማፂያኑ ወደሚቆጣጠሩት አካባቢ ርዳታም ሆነ ሌላ ቁሳቁስ እንዳይደርስ በየስፍራዉ ኬላ አቁሞ እየተቆጣጠረ ነዉ።

የሁለቱ ሱዳኖች ጉዳይ «ገለለልተኛ» አጥኚ የሚባሉት አጂና ኦጅዋንግ፥ የሱዳን መንግሥት በጦርነቱ ለተፈናቀለዉ ሕዝብ ርዳታ እንዳይደርስ መከልከሉ ዘር ከማጥፋት የሚቆጠር በመሆኑ መቀጣት አለበት ባይ ናቸዉ።
                       
«ወደ ደቡባዊ ኮርዶፋን የሚላክ ሰብአዊ እርዳታን ለማደናቀፍ የሚወሰድ ማናቸዉም እርምጃ በጦር ሐይል የሚያስቀጣ መሆኑን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ማረጋገጥ አለበት።ይሕን በማድረግም ድርጅቱ በአካባቢዉ በረራን ማገድና፥ የካርቱም መንግሥት ሚሳዬሎች ባካባቢዉ እንዳይተኮሱ መከልከል አለበት።»

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ኦጅዋንግ ያሉትን ርምጃም ሆነ ርዳታ ሰጪዎች የጠየቁትን መፈፀም መቻል-አለመቻሉ ላሁኑ አልየለትም። 

Refugees arrives at the Gendrassa camp in Maban, Upper Nile State, South Sudan, on the border with Sudan, August 1, 2012. According to the International Medical Corps, an estimated 120,000 refugees have fled violence and hunger in Sudan into camps in South Sudan. Approximately 1,000 refugees were transferred on Wednesday from Jamman camp to the newly constructed Gendrassa camp, where they receive health screenings and vaccinations at International Medical Corps' clinic. International Medical Corps has been providing primary health care, nutrition, and water/sanitation/hygiene services in South Sudan since 1994. REUTERS/Margaret Aguirre/International Medical Corps/Handout (SOUTH SUDAN - Tags: SOCIETY POLITICS CIVIL UNREST) FOR EDITORIAL USE ONLY. NOT FOR SALE FOR MARKETING OR ADVERTISING CAMPAIGNS. THIS IMAGE HAS BEEN SUPPLIED BY A THIRD PARTY. IT IS DISTRIBUTED, EXACTLY AS RECEIVED BY REUTERS, AS A SERVICE TO CLIENTS
እርዳታ ፈላጊዎችምስል Reuters
Logo des UN-basierten World Food Programme (WFP), undatiert, 2006 Welternährungsprogramm

ጀምስ ሺማንዩላ

ነጋሽ መሐመድ

ሒሩት መለሰ 

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ