የሰበታ ተፈናቃዮች ምሬት
ሰኞ፣ መጋቢት 9 2011ማስታወቂያ
ሰበታ ውስጥ ወለቴ ቀበሌ 03 ይገኙ የነበሩ መኖሪያ ቤቶቻቸው ህገ ወጥ ተብሎ በመፍረሱ ምክንያት የተፈናቀሉ ሰዎች ለከፋ ችግር መጋለጣቸውን አስታወቁ። እነዚሁ ከ4 ወር በፊት ቤታቸው የፈረሰባቸው ሰዎች ከ3 ሺህ በላይ መሆናቸውን በመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት መኢአድ ጽህፈት ቤት በሰጡት መግለጫ ላይ ተናግረዋል። ቤታቸው በመፍረሱ በአብያተ ክርስቲያን ተጠልለው እንደሚገኙ የተናገሩት እነዚሁ ሰዎች የሚበሉት እና የሚጠጡት እንደሌላቸው የልጆቻቸውም ትምሕርት መስተጓጓሉን በምሬት ገልጸዋል። መንግሥት እኛን ህገ ወጥ እያለ በህገ ወጥ መንገድ ሊያስተናግደን አይገባም የሚሉት እነዚሁ ተፈናቃዮች አፋጣኝ መፍትሄ እንዲፈለግላቸው ጠይቀዋል።
ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር
ኂሩት መለሰ
አዜብ ታደሰ