የሰብዓዊ መብቶች ጉባዔና ውዝግቡ
ረቡዕ፣ ጥቅምት 24 2003ማስታወቂያ
የሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ በሚል በአዲስ መልክ ስያሜውን ይዞ የቀጠለው የኢትዮዽያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ (ኢሠመጉ)፤ የባንክ ሂሳቤ ታገደብኝ ሲል በተለይ ለዶቸቬለ ገልጸ። ኢሠመጉ ከመንግስት አካል እንድጠቀም ተፈቅዶልኝ የነበረው ገንዘብ እገዳ የተጣለበት መሆኑ ስለተገለጸልኝ ወደፍርድ ቤት ልሄድ ነው ይላል። በአቢሲኒያ ባንክ ያለው የድርጅቱ ገንዘብ ስለመታገዱ የማውቀው ነገር የለም ይላል-የኢትዮዽያ የበጎ አድራጎት ድርጅቶችና ማህበራት ኤጀንሲ። የሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ ሰብሳቢ የሆኑት ወይዘሮ እልፍነሽ ደምሴ ከአቢሲኒያ ባንክ የተጻፈውን ደብዳቤ በማንበብ ይጀምራሉ....
መሳይ መኮንን
ነጋሽ መሐመድ