1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የሳዴክ ጉባኤ

ዓርብ፣ ጥር 3 2005

ስለ ጦር ስምሪቱ በግልጽ የሚታዬ ተግዳራቶች ቢኖሩም የደቡባዊ አፍሪቃ መንግስታት የልማት ማህበርሰብ ዋና ፀሐፊ ቶማስ ሳላማዖ እንደሚሉት ግን ሳዴክ ወታደሮቹን ያለ ምንም ዓለም አቀፍ እርዳታ ለማዝመት አቅዷል።«የዓለም አቀፉን ማህበረሰብ እርዳታ መጠበቅ የለብንም። በራሳችን አቅም መጀመር እንችላለን። የያዝነውን እንቀጥልበታለን።»

https://p.dw.com/p/17Ii7
Tanzania's President Jakaya Kikwete speaks during a press availability with Secretary of State Hillary Rodham Clinton at the State House in Dar es Salaam, Tanzania, Monday, June 13, 2011. (Foto:Susan Walsh, POOL/AP/dapd)
የጉባኤዉ አስተናጋጅ ኪክዌቴምስል dapd

የደቡባዊ አፍሪቃ መንግስታት የልማት ማህበርሰብ በምህጻሩ ሳዴክ አባል ሀገራት ትናንት በታንዛኒያ ማካሄድ በጀመሩት ስብሰባ በምስራቅ ዲሞክራሲያዊ ኮንጎ ሪፐብሊክ፣ በማዳካስካር እየታዬ ስላለው የፖሊቲካ ቀውስና ስለዚምባቢዌ ሁኔታ መክረዋል። በዚህም መሠረት በዲሞክራሲያዊ ኮንጎ የሳዴክን የተጠንቀቅ ጦር የማዝመት ሂደት መጀመሩ ተገልጿል። ነገር ግን ካለኮንጎ መንግስትና ከM23 አማጺያን ተሳታፊነት ውጭ የተደረገው የሳዴክ ምክክር ያማሬ ውጤት ማምጣቱ አጠራጥሯል። ገመቹ በቀለ ዝርዝር ዘገባ አለው።

በዲሞክራሲያዊ ኮንጎ ሪፐብሊክ ስለሚታየው ግጭት እንዲሁም በማዳካስካሪና ዚምባቡዌ እየታየ ስላለው የፖሊቲካ ቀውስ የደቡባዊ አፍሪቃ መንግስታት የልማት ማህበርሰብ ሳዴክ ትናንት በጀመረው ጉባዔ ላይ የአስተናጋጇ ሀገር የታንዛኒያ ፕሬዚዳንት ጃካያ ኪክዌ፣ የደቡብ አፍሪቃ አቻቸውናን የናሚቢያ አቻዎቻቸው ጄኮብ ዙማና ሂፊኬፑኜ ፓሃምባ እንዲሁም የሞዛምቢክ ፕሬዚደንት አርማንዶ ኤሚልዮ ገቡዛም ተገኝተዋል።

ሳዴክ ከወር በፊት በታንዛኒያ ባደረገው ስብሰባ በምስራቅ ዲሞክራሲያዊ ኮንጎ ሪፐብሊክ የተሰማራውን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ሰላም አስከባሪ ኃይልን ለማጠናከር የራሱን የጦር ኃይል ለመላክ መወሰኑ ይታወሳል። ትናንት በተጀመረው ስብሰባም አንዱ ዓላማ ከዚህ ውሳኔ ወዲህ ምን እንደተሰራ ለመገምገም እንደሆነ ተነግሯል። ባለፈው ታህሳስ በተደረገው የሳዴክ ስብሰባ አባል ሀገራቱ 4000 ወታደሮችን ወደ ምስራቅ ዲሞክራሲያዊ ኮንጎ ሪፐብሊክ ለመላክ ቃል ቢገቡም፣ የጦር ኃይሉን ወደ ሥፍራው የማዝመቱ ሥራ አስቸጋሪ እንደሚሆን ያካባቢው የፖሊቲካ ተንታኙ ጀነራሊ ኡሊምዌንጉ ይናገራሉ

«ጦር ማዝመትን በተመለከት በርግጠኝነት ፈተናዎ ች ይኖራሉ። ስለጉዳዩ በቂ መረጃ እውቀት ያላቸው አይመስለኝም። እንዴት አስተዋጽዖ ማድረግ እንደሚቻል የተቀመጠ ግልጽ ነገር የለም። በዲሞክራሲያዊ ኮንጎ ሪፐብሊክ ብዙ የማይታወቁ ጉዳዮች አሉ። ይህ ደግሞ ጦር ስምሪቱ ግልጽ የሆነ ያልሆነ አካሄድ እንዲኖረው ያደርጋል። ብዙ ችግሮችና መሰናክሎች አሉት።»

ስለ ጦር ስምሪቱ በግልጽ የሚታዬ ተግዳራቶች ቢኖሩም የደቡባዊ አፍሪቃ መንግስታት የልማት ማህበርሰብ ዋና ፀሐፊ ቶማስ ሳላማዖ እንደሚሉት ግን ሳዴክ ወታደሮቹን ያለ ምንም ዓለም አቀፍ እርዳታ ለማዝመት አቅዷል።

«የዓለም አቀፉን ማህበረሰብ እርዳታ መጠበቅ የለብንም። በራሳችን አቅም መጀመር እንችላለን። የያዝነውን እንቀጥልበታለን።»

የታላላቆቹ ኃይቆች አከባቢ ዓለም አቀፍ ጉባዔ በምስራቅ ዲሞክራሲያዊ ኮንጎ ሪፐብሊክ ዓለም አቀፍ ለዘብተኛ የጦር ኃይል እንዲቋቋም ካለፈው ሐምሌ ጀምሮ ሙከራ ሲያደርግ ቆይቷል። ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ኮንጎም የዚው ጉባኤ አባል ናት። አንዳንድ የአከባቢው ሀገራት የሳዴክ አባል ሀገራት ቢሆኑም በሳዴክና በታላላቆቹ ኃይቆች አከባቢ ዓለም አቀፍ ጉባዔ መካከል ዲሞክራሲያዊ ኮንጎ ሪፐብሊክን በተመለከተ ግልጽና ተደጋጋፊ መዋቀራዊ አሰራር የለም።

ይህ የታንዛኒያ ስብሰባ እየተካሄደ ባለበት ባሁኑ ጊዜ በዩጋንዳ መዲና ካምፓላም የኮንጎ ፕሬዚደንት ካቢላን መንግስትና የM23 አማጺያንን ለማስታረቅ የሰላም ድርድር እየተካሄደ ነው። እንዲህ የሆነ የተናጠል አሰራር ችግር አለው የፖሊቲካ ተንታኙ ጀነራሊ ኡሊምዌንጉን ይላሉ፤

«ቅንጅት የለም። በሁለቱም ሂደቶች መካከል የመረጃ ፍሰት የለም። ማለትም፣ በምስራቅ ኮንጎ የቀጠለውን ውዝግብ በተመለከተ በካቢላ መንግስትና በM23 አማጺያን መካከል በሚካሄደው ድርድር ላይ ነው ጥረቱ ማትኮር ያለበት። የዲሞክራሲያዊ ኮንጎ ሪፐብሊክ ችግር የሚያሳስበን ከሆነ ከነዚህ ሁለቱ ጋር ነው ሌሎች አንድ ላይ መስራት ያለባቸው። ሁለቱ ቡድኖች አሁን ካምፓላ ውስጥ እያደረጉ ያሉትን ድርድር ያላገናዘበ ማንኛውም መፍትሔ አፈላላጊ የሚመስል ሂደት ሊኖር አይገባም።»

በሳዴክና በታላላቆቹ ኃይቆች አከባቢ ሀገራት መካከል ያለው የመረጃ ፍሰት ቢጠብም ሳዴክ ባለፈው ታህሳስ በወሰነው ውሳኔ መሰረት የተጠንቀቅ ጦርን ለመላክ እየተዘጋጀ ነው። በዚህ ጉዳይም ላይ በሁለቱ ቡድናት መካከል ንግግር ይካሄዳል ይላሉ የሳዳክ ዋና ፀኃፊ ቶማስ ሳላማዖ፣

«ይህ በሂደት የሚሰራ ጉዳይ ነው። በታላላቁ ኃይቆች አከባቢ ከሚኖሩ ወዳጆቻችን ጋር አንድ ላይ መነጋገር አለብን። አፍሪቃ ህብረትንም ማጠቃለል አለብን። ወደ ፊት እንራመዳለን።»

በዚህ በታንዛኒያ እየተካሄድ ባለው የደቡባዊ አፍሪቃ ሀገራት ጉባኤ ላይ ሶስት ዓመት የሆነውን የማዳካስካር የፖለቲካ ውዝግብ ስለሚያበቃበት እና ስለዚምባቡዌየፖሊቲካ ጉዳይም ተነስቷል። በሁለቱ ሀገራት ሊካሄዱ የታቀዱ ብሔራዊ ምርጫዎች ዋናው የውይይቱ ጉዳይ መሆኑ ታውቋል።

ARCHIV - Der damalige Oppositionsführer und jetzige Präsident auf der Tropeninsel Madagaskar, Andry Rajoelina (Archivfoto vom 17.03.2009) posiert umringt von Soldaten nach der Erstürmung des Präsidentenpalastes in Antananaarivo. Ein meuternder Oberst der Armee von Madagaskar hat schwere Vorwürfe gegen einheimische Unternehmen sowie indische und pakistanische Geschäftsleute erhoben: Sie sollen laut Oberst Charles Andrianasoavina den Putsch in Madagaskar im Frühjahr 2009 mit 12,2 Milliarden Ariary (4,5 Millionen Euro) finanziert haben. Der nach einem erneuten Umsturzversuch im vergangen November festgenommene Offizier will offenbar als eine Art Kronzeuge gegen die Regierung von Präsident Andry Rajoelina auftreten. EPA/KIM LUDBROOK (zu dpa 0091 «Offizier als Kronzeuge: Pakistaner und Inder bezahlten Putsch» am 22.01.2011) +++(c) dpa - Bildfunk+++
የማዳጋስካሩ መሪ-ራጆሊናምስል picture-alliance/dpa
Congolese M23 rebels withdraw on December 1, 2012 from the city of Goma in the east of the Democratic Republic of the Congo. Hundreds of Congolese M23 rebels began a withdrawal on December 1 from Goma as promised under a regionally brokered deal, after a 12-day occupation of the city. Around 300 rebels, army mutineers who seized Goma last week in a lightning advance, were seen by an AFP reporter driving in a convoy of looted trucks north out the main town in Democratic Republic of Congo's mineral-rich east. AFP PHOTO/PHIL MOORE (Photo credit should read PHIL MOORE/AFP/Getty Images)
የኮንጎ አማፂያን M23ምስል Phil Moore/AFP/Getty Images

ገመቹ በቀለ

አርያም