የሴት ልጅ ግርዛትና ጀርመን
ማክሰኞ፣ የካቲት 1 2003ማስታወቂያ
ዓለም ዓቀፉ የስደተኞች ጉዳይ ተከታታይ ተቋም IMO እንደሚለዉ ይህ የሰለጠነዉ ዓለም ባህል አካል ያልሆነዉ ተግባር ወደአዉሮፓና ሰሜን አሜሪካ የዘለቀዉ በተበራከተዉ ስደት ምክንያት ነዉ። የሴቶችን ሰብዓዊ መብት ከመጣስ የሚቆጠረዉ ግርዛት ዛሬ ዛሬ በአፍሪቃና ሌሎች ጎጂ ባህላዊ ድርጊቶችን በሚዘወተርባቸዉ አካባቢዎች ብቻ ሳይሆን ወደጀርመንና ሌሎች የአዉሮጳ አገራትም እየተሻገረ መሆኑ ተሰምቷል። ጀርመን ዉስጥ የዚህ ችግር ሰለባዎችን በስልክ የማማከር አገልግሎት መስጠት ተጀምሯል።
ናዲያ ባኤፋ
ሸዋዬ ለገሠ
አርያም ተክሌ