1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የስርጭት ጊዜ ለውጥ

ማክሰኞ፣ መጋቢት 20 2003

ዶቼቬለ የአማርኛ አገልግሎት፥- የበርካታ አድማጮቹን ጥያቄ ከግምት በማስገባት እና በቅርቡ ኢትዮጵያ ውስጥ በጉዳዩ ላይ የተደረገውን ጥናት በመመርኮዝ የስርጭት ጊዜ ለውጥ ያደርጋል ።

https://p.dw.com/p/R5jA

በዚሁ መሰረት ከመጪዉ እሁድ መጋቢት 18 እስከ ሚያዚያ 1: 2003 ድረስ ከቀኑ 11 :00 እስከ 12 ሠዓት በአጭር ሞገድ የሚተላለፈዉ ስርጭታችን ከምሽቱ 1:00 ሠዓት እስከ ምሽቱ 2:00 ሠዓት ድረስ በድጋሚ ይሰራጫል።ከሚያዚያ ሁለት 2003 ጀምሮ ግን የቀኑ ስርጭት ሙሉ በሙሉ ቆሞ ሁሉም ዝግጅታችን ከምሽቱ አንድ ሠዓት እስከ ሁለት ሠዓት ባለዉ ጊዜ ይሰራጫል።ከ1957 አንስቶ በራድዮ የሚያሰራጨው ዶቼቬለ በዘመኑ ቴክኖሎጂም ከአድማጮቹ ይደርሳል ።ማንኛውም አድማጭ ዝግጅቶቹን በድረ ገፅ፣ በፖድካስት፣ በፌስ ቡክ እና በትዊተርም መከታተል፣ መሳተፍም ይችላል።

ዓለምን ለመረዳት ዶቼቬለን ያድምጡ