1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የሶማሊያ ሁኔታና ኢትዮጵያ

ማክሰኞ፣ መስከረም 15 2005

ሶማሊያ የዘመተዉ የአፍሪቃ ሕብረት ጦር (አሚሶም)ና የሶማሊያ መንግሥት ወታደሮች የአክራሪዉ ደፈጣ ተዋጊ ቡድን የአሸባብ የመጨረሻ ትልቅ ይዞታ ኪስማዮን ለመቆጣጠር የከፈቱት ጥቃት እንደቀጠለ ነዉ።

https://p.dw.com/p/16E1A
Transitional Federal Government soldiers on their truck in Bur Haqaba, 60 kilometers (37 miles) south of Baidoa, Somalia Thursday, Dec 28, 2006. Residents living south of Mogadishu said they saw convoys of Islamists driving south toward the port city of Kismayo. In Mogadishu, gunfire echoed through the streets and hundreds of gunmen, who just hours earlier fought for Quranic rule, took off their Islamic uniforms and submitted to the command of clan elders, an AP reporter in Mogadishu said. Some clan militiamen began looting Islamic courts' bases and buildings belonging to Islamic courts officials, witnesses said. (AP Photo/Guy Calaf/pool)
የሶማሊያ መንግስት ጦርምስል AP

ኬንያ መራሹ ጦር ባለፈዉ ሳምንት ከኪስማዮ አርባ ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ እንደሚገኝ ቢያስታዉቅም እስካሁን ሥልጣዊቱን የወደብ ከተማ ከአሸባብ እጅ አላስለቀቀም።ሶማሊያ የሠፈረዉ የኢትዮጵያ ጦር ግን በኪስማዩዉ ዘመቻ በቀጥታ አልተካፈለም።አሸባብ በተለያዩ አካባቢዎች የሚፈፅመዉ ጥቃትም እንደቀጠለ ነዉ። የሶማሊያን ወቅታዊ ሁኔታና የኢትዮጵያን ተሳትፎ በተመለከተ ነጋሽ መሐመድ የኢትዮጵያ ዉጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲን አነጋግሮ ያጠናቀረዉ ዘገባ አለ።


የኬንያ ጦር አምና ጥቅምት ኪስማዮን ለመያዝ የነደፈ ዕቅዱን ባመቱ ዘንድሮ ገቢር ለማድረግ ከሌሎች ሐገራት የዘመቱትን (የአሚሶም)ና የሶማሊያ መንግሥት ወታደሮችን አስከትሎ ወደ ወደብ ከተማይቱ መንቀሳቀሱን ካስታወቀ ሳምንቱ።

ቤይዶዎንና በለድወይንን የመሳሰሉትን የደቡብ ሶማሊያን ሥልታዊ ከተሞችን ከሐቻምና ክረምት ጀምሮ የሚቆጣጠረዉ የኢትዮጵያ ጦር ግን እንደ ኬንያ ብጤዉ በአሚሶም ዕዝ ሥር አልተጠቃለለም።በኪስማዩዉ ዘመቻም አልተከፋለም።አምባሳደር ዲና ሙፍቲ እንደሚሉት ጦሩ ላሁኑ በቀጥታ ኪስማዮ አይዝመት እንጂ አስፈላጊ ከሆነ መዝመቱ አይቀርም።

የአሚሶም ጦር ኪስማዮ ለመድረስ አርባ ኪሎ ሜርትር እንደቀረዉ ባለፈዉ ሳምንት መጀመሪያ ላይ ሲነገር ከተማይቱን ለቀዉ የነበሩት የአሸባብ ተዋጊዎች ባንድ ቀን ልዩነት ተመልሰዉ ከተማይቱን ተቆጣጥረዋታል።

የአሸባብ አባላት ወይም ተባባሪዎቹ የሚባሉ አጥፍቶ ጠፊዎችና ታጣቂዎች ርዕሠ-ከተማ ሞቃዶሾ ዉስጥ የሚጥሉት አደጋም እየተደጋገመ ነዉ።ሰሞኑን በተጣሉ አደጋዎች ሰወስት ጋዜጠኞችንና አንድ የምክር ቤት እንደራሴን ጨምሮ ሃያ ሰዎች ተገድለዋል።አምባሳደር ዲና እንደሚሉት አሸባብ በወታደራዊዉም በፖለቲካዉም መስክ እየተሸነፈ ነዉ።መፍጨርጨሩ ግን ወደፊትም አይቀርም።


አምባሳደር ዲና ከሳምንት በፊት አዲሱ የሶማሊያ ፕሬዝዳት ሐሰን ሼኽ መሐሙድ ሥልጣን በተረከቡበት ሥነ-ሥርዓት ላይ ከአዲሱ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚንስትር ጋር ሆነዉ የተገኙተዉ ነበር።በሞቃዲሾዉ ሥነ-ሥርዓት ላይ የበርካታ ሐገራት ተወካዮች መገኘታቸዉ አምባሳደሩ እንደሚያምኑት አዲሱ የሶማሊያ መንግሥት ሠፊ ድጋፍ እንዳለዉ ጠቋሚ ነዉ።

በሶማሊያም፥ በኢትዮጵያም በተመሳሳይ ጊዜ አዳዲስ መሪዎች ሥልጣን መያዛቸዉ የሁለቱን ሐገራት ግንኙነት አምባሳደሩ እንደሚሉት ይበልጥ ያጠናክረዋል እንጂ አይለዉጠዉም።ኢትዮጵያም ለአዲሱ ፕሬዝዳትና ለመንግሥታቸዉ ሙሉ ድጋፏን ትሰጣለች።

አዲሱ የሶማሊያ ፕሬዝዳት ለዘብተኛ ከሚባሉት የአሸባብ መሪዎች ጋር ለመደራደር ማቀዳቸዉን በተመረጡ ማግሥት አስታዉቀዉ ነበር።አንድ የአሸባብ ሹም ትናንት እንዳሉት ግን የአዲሱን መንግሥት ሹማምንታት የምክር ቤት አባላትን አንድ በአንድ ይገድላል።
ነጋሽ መሐመድ
ሸዋዬ ለገሠ

Somali government soldiers patrol the scene of an explosion in the capital of Mogadishu September 12, 2012. Somalia's al Shabaab rebels carried out a bomb attack on Wednesday that targeted a Mogadishu hotel where the president and Kenya's visiting foreign minister were holding a news conference, the group said. REUTERS/Omar Faruk (SOMALIA - Tags: CIVIL UNREST POLITICS SOCIETY)
በአዲሱ ፕሬዝዳንት ላይ ከተቃጣዉ የግድያ ሙከራ በኋላምስል Reuters
Residents walk past the campaign billboard of Somalia's presidential candidate Hassan Sheikh Mohamud in Somalia's capital Mogadishu, September 9, 2012. Somalia's lawmakers voted overwhelmingly on Monday for Mohamud as the country's next president, with the streets of the capital erupting into celebratory gunfire, Reuters witnesses said. Two of the four candidates who made it to the second round of voting opted out, leaving the incumbent President Sheikh Sharif Ahmed and Mohamud.Picture taken September 9, 2012. REUTERS/Feisal Omar (SOMALIA - Tags: POLITICS ELECTIONS)
አዲሱ ፕሬዚዳንት ሐሰን ሼኽ መሐሙድምስል picture-alliance/dpa
ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ