የሶማሊያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሥልጣን መልቀቅ
ሰኞ፣ ሰኔ 13 2003ማስታወቂያ
አብዱላሂ ትናንት እንደተናገሩት ከስራ ለመሰናበት የወሰኑት ለሶማሊያውያን ጥቅም ሲሉ እና የሶማሊያን ወቅታዊ ሁኔታ ግምት ውስጥ በማስገባት ነው ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሥልጣን የወረዱት የሶማሊያው ፕሬዝዳንትና የሶማሊያ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ካምፓላ ውስጥ በተካሄደ ድርድር በሃገሪቱ ምርጫ የሚካሄድበትን ጊዜ ለማረዘም ስምምነት ላይ ከተደረሰ በኃላ ነው ። የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሼክ ሸሪፍ ሼክ አህመድና የፓርላማው አፈ ጉባኤ ሸሪፍ ሀሰን ሼክ አደን የሶማሊያውን ምርጫ ለማራዘም ካምፓላ ኡጋንዳ ውስጥ ስምምነት ላይ የደረሱት ባለፈው ሐሙስ ነበር ።
ሂሩት መለሰ
አርያም ተክሌ