1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የሶማሌ ክልል ር/መስተዳድር ለተፈናቃዮች ያደረጉት ጥሪ

እሑድ፣ ታኅሣሥ 8 2010

በኦሮሚያና በሶማሌ ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች ከወራት በፊት አንስቶ ግጭት ተከስቶ እንደነበር ይታወሳል። በሁለቱ ክልሎች መካከል ያለው ወሰን በትክክል ባለመለታየቱ በተነሳው ግጭት በሁለቱም ክልሎች በመቶዎች የሚገመቱ ሰዎች ሕይወት መጥፋቱ እና በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩም መፈናቀላችው ይታወቃል።

https://p.dw.com/p/2pSIy
Äthiopien Flüchtlinge vor ethnischer Gewalt
ምስል DW/J. Jeffrey

«ይህ ሁሉ ሰው ሲፈናቀል የፌዴራል መንግሥት የት ነበር?»

በኦሮሚያና በሶማሌ ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች በተከሰተው ግጭት የተፈናቀሉ የኦሮሞ ተወላጆች ወደነበሩበት እንዲመለሱ የሶማሌ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ አብዲ መሐመድ ኡመር ከጥቂት ቀናት በፊት ጥሪ አቅርበዋል። ተፈናቃዮች ወደ ሶማሌ ክልል እንዲመለሱ የቀረበው ጥሪ በርግጥ ተግባራዊ ሊሆን የሚችል ነው አይደለም፣ እንዲመለሱ የሚያስችሉ ሁኔታዎች አሉ የሉም ፣ እነዚህ ጥያቄዎች ብዙ እያነጋገሩ ነው። በዚሁ ጉዳይ ላይ እኛም ውይይት አካሂደንበታል።

አርያም ተክሌ

ማንተጋፍቶት ስለሺ