የሶማሌ ክልል ድጎማ
ሐሙስ፣ ግንቦት 29 2011ማስታወቂያ
የሶማሌ ክልል መስተዳድር ባለፈዉ ዓመት ኃምሌ ጅግጂጋ ከተማ ዉስጥ በደረሰ ጥቃት ሐብት ንብረታቸዉ ለጠፋ ወይም ለተዘረፈባቸዉ የከተማይቱ ነዋሪዎች ድጎማ መስጠት ጀመረ።ድጎማዉን ያገኙት የከተማይቱ ነዋሪዎች እንደሚሉት መስተዳድሩ የገንዘብ ድጎማ ከማድረጉ በላይ ችግራቸዉን በመረዳቱ ይበልጥ ደስተኛ ናቸዉ።መስተዳድሩ በጥቃቱ ለተገደሉ ቤተሰቦችና የአካል ጉዳት ለደረሰባቸዉም ድጎማ እንደሚሰጥ አስታዉቋል።መስተዳድሩ ለጉዳተኞች መደጎሚያ 100 ሚሊዮን ብር መመደቡን አስታዉቋልም።
መሳይ ተክሉ
ነጋሽ መሐመድ
ማንተጋፍቶት ስለሺ