1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የሶሪያ ወዳጆች ጉባኤ በኢስታንቡል

ሰኞ፣ መጋቢት 24 2004

የሶሪያ ወዳጆች ዓለምአቀፍ አገናኝ ቡድን ትናንት በቱርክ- መዲና ኢስታምቡል ለሶሪያ ችግር መፍትሄ ሲሻ ውሏል። ቱርክ የተመድ የፀጥታዉ ምክር ቤት ለተባባሰዉ የሶርያ ግጭት አንዳች ዉሳኔ ካላሳለፈ የሶርያ ህዝብ ራሱን ሊከላከል ይገደዳል ስትል፤

https://p.dw.com/p/14Wcu
Turkey's Prime Minister Tayyip Erdogan (R) meets with members of the opposition Syrian National Council (SNC) in Istanbul March 31, 2012. REUTERS/Murad Sezer (TURKEY - Tags: POLITICS)
የሶሪያ ወዳጆች ጉባኤ በኢስታንቡልምስል Reuters

የሶሪያ ወዳጆች ዓለምአቀፍ አገናኝ ቡድን ትናንት በቱርክ- መዲና ኢስታምቡል ለሶሪያ ችግር መፍትሄ ሲሻ ውሏል።  ቱርክ የተመድ የፀጥታዉ ምክር ቤት ለተባባሰዉ የሶርያ ግጭት አንዳች ዉሳኔ ካላሳለፈ የሶርያ ህዝብ ራሱን ሊከላከል ይገደዳል ስትል፤

የጀርመኑ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጊዶ ቬስተርቬለ ጀርመን የሶሪያን ቀዉስ ለመፍታት የፖለቲካ መፍትሄ እንዲፈለግ እንደምትመርጥ ለጉባኤዉ አመልክተዋል።

ከትናንቱ የኢስታምቡል የሶሪያ ወዳጆች ዓለምአቀፍ ጉባኤ መገንዘብ የሚቻል ሁለት ነጥቦች አሉ።  በመጀመሪያ ለሶሪያ ዓመጽ በዲሞክራሲያዊ መልኩ መፍትሄ የማግኘቱ ሁኔታ እየቀነሰ መሆኑንን እና በሁለተኛ ደረጃ ደግሞ አንዳንድ አገሮች ጠቀም ያለ ገንዘብ በማሰባሰብ የሶሪያ መንግስት ተቃዋሚያንን መርዳት እንደሚፈልጉ ነው።  የባህረ ሰላጤ አካባቢ የሚገኙ አገራት ማለትም እንደ ሳውድ አረቢያ፣ ካታር እና የተባበሩት የአረብ ኢሚራቶች በ200 ሚሊዮን ዶላር የሶሪያ መንግስት ተቃዋሚዎችን ለመደገፍ አስበዋል። ገንዘቡም  ከሶርያ መንግስት ጦር ከድተዉ በተቃውሞ ወገን ለተሰለፉ ወታደሮች ደሞዝ መክፈልን ጨምሮ ሥራ ላይ እንዲዉል የታሰበ ነዉ። ጉባኤው ላይ የተገኙ የሶርያ ብሄራዊ ምክር ቤት ተቃዋሚ ፖለቲከኞች ግን በግልፅ ገንዘቡ የጦር መሳሪያ ሊገዛበት እንደሚችል ሲናገሩ ተደምጧል።

ሶርያ ዉስጥ የሰብዓዊ መብት ጥሰቱ መባባሱ ትዕግስቷን እንደጨረሰዉ ያመላከተችዉ የጉባኤዉ አስተናጋጅ ሀገር-ቱርክ ደግሞ ሩሲያና ቻይናን ጨምሮ የተመ የፀጥታዉ ምክር ቤት  ይህን ቀዉስ ለመግታት ርምጃ የማይወስድ ከሆነ የሶርያ ህዝብ ራሱን ለመከላከል ይገደዳል ስልት ተደምጣለች። ጠቅላይ ሚኒስትር ሬቼፕ-ታይፕ-ኤርዶሃን በጉባኤው ማጠቃለያ «የሶሪያ ሁኔታ ክፉኛ አሳሳቢ ነው፤ የዘር ጭፍጨፋው እና ግድያው እንዲያበቃ የተቻለንን ሁሉ እናደርጋለን»ነዉ ያሉት። አክለውም ፤ « ዛሬ 83 አገሮች እና አለም አቀፍ ድርጅቶች -ሌሎች አገሮች ለሰው ልጅ ክብር እንደሚታገሉት ሁሉ- የሶሪያ ህዝብን ፍላጎት እና ጥያቄ ደግፈዋል።»

Supporters of Syrian President Bashar al-Assad run for cover as Turkish riot police use tear gas against them during a demonstration outside the "Friends of Syria" conference in Istanbul April 1, 2012. Turkish Prime Minister Tayyip Erdogan said the "legitimate demands of the Syrian people must be met, right here, right now" as Western and Arab countries met in Istanbul on Sunday to try to agree on how to support armed rebels fighting to unseat President Bashar al-Assad. Erdogan was addressing a meeting of mostly foreign ministers from around 70 countries including the United States and leading European Union and Gulf powers who call themselves the "Friends of Syria". Assad's forces pounded a pro-opposition neighbourhood of Homs city with artillery fire and mortars on Saturday, as his crackdown continued a day after the Syrian Foreign Ministry announced that the year-old revolt was over. REUTERS/Murad Sezer (TURKEY - Tags: POLITICS CIVIL UNREST)
ምስል Reuters

የጀርመን ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጊዶ ቬስተርቬለ ፤ ሶርያ ዉስጥ የመንግስት ኃይሎች የሚወስዱት የኃይል ርምጃ መባባሱን ቢጠቁሙም ሀገራቸዉ ከምንም በላይ ለሶርያ ቀዉስ ፖለቲካዊ መፍትሄ እንዲፈለግ እንደምትመርጥ ነዉ ያመለከቱት።

«ሶሪያ ዉስጥ የሚወሰደዉ የኃይል ርምጃ ሊታገሱት ከማይቻልበት ሁኔታ ላይ ነዉ። ይህ የኃይል ርምጃ እንዲቆም ሁላችንም በጋራ ሆነን መስራት አለብን። ለዚህ ሁላ ጥቃት አንድ ተጠያቂው ነው ያለው። ይኸውም የአሳድ አገዛዝ ነው። የተባበሩት መንግስታትም ሆኑ የአረብ ሊጉ፤ ኮፊ አናንን የሶሪያው ልዩ መልዕክተኛ አድርገው መርጠው ፖለቲካዊ መፍትሄ መፈለጋቸው ትክክል ነው። እኛ ጀርመኖች የምንፈልገዉና የምንደግፈዉ ፖለቲካዉ መፍትሄ ነዉ፤ ስለዚህም የኮፊ  አናን ባለስድስት ነጥብ መርሃ ግብር ድጋሚ እድል እንዲሰጠዉ እንሻለን።»

ዩናይትድ ስቴትስ በበኩሏ የሶርያ መንግስት ተቃዋሚ ኃይሎችን በዘመናዊ የመገናኛ መሣሪያዎች ለመርዳት ፍላጎቷን ኢስታንቡል ላይ አመላክታለች።  የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሂለሪ ክሊንተን  የሶሪያ  መንግስት ከእንግዲህ በአማፂያኑ እና በመንግስት ተቃዋሚያን ላይ ጥቃት የሚያደርስ ከሆነ መንግስቱ ላይ ከፍትኛ ርምጃም ሊጣል እንደሚችል  አስጠንቅቀዋል።

U.S.Secretary of State Hillary Rodham Clinton speaks with an Arab official as she arrives to join foreign ministers from dozens of countries gathered to set conditions for a new Syria, pushing for tighter sanctions and diplomatic pressure to further isolate President Bashar Assad, while urging the opposition to offer a democratic alternative to his regime, in Istanbul, Turkey, Sunday, April 1, 2012. The show of solidarity at the Friends of the Syrian People conference in Istanbul, was marred by the absence of China, Russia and Iran, key supporters of Assad who disagree with Western and Arab allies over how to stop the bloodshed.(Foto:AP/dapd)
ምስል AP

« ኮፊ አናን ይህን ቀዉስ እንድንፈታ መርሃ ግብር ሰጥተውናል። ባሸር-አል-አሣድ የእሳቸዉን ተማፅኖ ለመቀበል እስካሁን አሻፈረኝ ብለዋል።  ምክንያት ለመስጠት ወይም  ለማጓተት ምንም ጊዜ የለም።  ጊዜው የእውነታ ነው። »ስለሆነም በሶሪያ መንግስት ላይ ለሚደረገው ርምጃ የሚቀጥሉት ሳምንታት ወሳኝ ናቸው። የሶሪያ ወዳጆች ጉባኤ  ፈረንሳይ - ፓሪስ ዉስጥ  በቅርቡ በቀጣይ  ይካሄዳል። ቢያንስ በፓሪሱ ጉባኤ በተግባር የሚዉል ውሳኔ ላይ መደረስ እንደሚገባል አንድ የሶሪያ ተቃዋሚ ቡድን ተወካይ ጠይቀዋል። ሌሎች የሶሪያ የተቃዋሚ ቡድን ተወካዮችም በበኩላቸዉ የምዕራቡ አገሮች የሶርያን ቀዉስ ለማብቃት የአየር ጥቃት ማድረጋቸዉ አስፈላጊ እንደሚሆን ለጉባኤው  ተናግረዋል። ከትናንቱ የሶሪያ ወዳጆች ጉባኤ በኋላ የሶሪያ ጉዳይ ይበለጥ የተጧጧፈ መስሏል።

ልደት አበበ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ