1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የሶሪያ ጦርነትና ዲፕሎማሲዉ

ሐሙስ፣ ታኅሣሥ 4 2005

አማፂያኑ ያገኙት ዕዉቅና የእልቂት፥ ጥፋት፥ ዉድመቱን ግመት አናረዉ እንጂ አላረገበዉም።ጥንታዊቱን ሐገር ወደ ትቢያ መከመሪያነት ቀየራት-እንጂ የአረብ ሊጉ መሪ እንዳሉት አማፂያኑን የደማስቆ ቤተ-መንግሥትን ከሚቆጣጠሩበት ደረጃ አላቃረባቸዉም።

https://p.dw.com/p/1724n
Bundesaußenminister Guido Westerwelle (FDP, r) unterhält sich am 12.12.2012 auf der Konferenz der "Freunde des syrischen Volkes" in Marrakesch (Marokko) mit seinem Amtskollegen aus den Vereinigten Arabischen Emiraten Scheich Abdullah bin Zayid Al Nahyan. Foto: Tim Brakemeier/dpa pixel Schlagworte .Konflikte , .International , .Syrien , Konferenz , Freundesgruppe
የሶሪያ «ወዳጆች» ጉባኤ-ማራኪሽምስል picture-alliance/dpa

13 12 12


የሶሪያ ፖለቲካዊ ዉዝግብ ከዲፕሎማሲያዊዉ መፍትሔ ይልቅ በጦርነቱ ዉድመት እንደቀጠለ ነዉ።ትናንት ማራኪሽ-ሞሮክ የተሰበሰቡት የምዕራባዉያንና የአረብ ሐገራት መልዕክተኞች የፕሬዝዳት በሽር አል-አሰድን መንግሥት ለሚወጉት አማፂያን እዉቅና መስጠታቸዉ ለአማፂያኑ እንደ ዲፕሎማሲያዊ ድል ታይቷል።የሶሪያ መንግሥትን ትደግፋለች የምትባለዉ ሩሲያ ግን በተለይ ዩናይትድ ስቴትስ ለአማፂያኑ ዕዉቅና መስጠቷን አጥብቃ ተቃዉማዋለች።ለአማፂያኑ ዕዉቅና መሰጠቱም ሆነ ተቃዉሞዉ ሶሪያን የሚያወድመዉን ጦርነት የመለወጥ አዝማሚያ አላሳየበትም።ነጋሽ መሐመድ አጭር ዘገባ አለዉ።

ጦርነቱ ቀጥሏል።መንደሮች፥ አነስተኛ ከተሞች፥ መንገድ-ማሳዎችን እያወደመ፥ ከታሪካዊያኑ ትላልቅ ከተሞች አሌፖን ደፍጥጦ፥ ደማስቆን ባለፍ-አገደምም ቢሆን እያንቀረቀባት ነዉ።ሃያ-አንደኛ ወሩ።በትንሽ ግምት አርባ ሺሕ ሕዝብ አልቋል።የቆሰለዉ በብዙ መቶ ሺሕ ይገመታል።ከግማሽ ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ተሰድዷል።በሚሊዮን የሚቆጠር ሕዝብ ከወደመ፥ ወይም በከፊል ከጠፋ ቤን ንብረት፥ ቀዬዉ ተፈናቅሏል።


እንደ ሶሪያ የታሪክ ዘመን ብዛት እብዙ ቦታ የተሰነጣጠቁት አማፂያን ከዚሕ ቀደም የመሠረቱትን ሕብረት አፍርሰዉ በቅርቡ አዲስ መመሥረታቸዉ-አንድ፥ ትናንት ማራኪሽ-ሞሮኮ የተሰበሰቡትን የዓረብ እና የምዕራብ ሐገራትን ዕዉቅና ማግኘታቸዉ-ሁለት፥ምክንያት የሚጠቅሱት-እራሳቸዉ አማፂያኑና አደራጆቻቸዉ እንደሚሉት ለነሱ የድል-ጭላጭል ብርቀት፥ ለአሰድ ስርዓት የዉድቀት ምልክት ነዉ።

የአረብ ሊግ ዋና ፀሐፊ ነቢል ኤል አራብይ ትናንት እንዳስታወቁት ደግሞ ሊጋቸዉ የሚደግፋቸዉ አማፂያን በዲፕሎማሲዉ ብቻ ሳይሆን በጦር አዉዱም ከድል አፋፍ ላይ ናቸዉ።

«አዲስ ብሔራዊ አመራር አለን።አዲስ ወታደራዊ አመራር አለን።በዚሕ መሐል ዉጊያዉ ደማስቆ ደርሷል።ይሕ አሁን ያለዉ ሥርዓት ከፍፃሜዉ ከሚደርሰዉ የመጨረሻ ፉሮጎ ላይ መሳፈሩን አመልካች ነዉ።»

ይሁን እንጂ አማፂያኑ ያገኙት ዕዉቅና የእልቂት፥ ጥፋት፥ ዉድመቱን ግመት አናረዉ እንጂ አላረገበዉም።ጥንታዊቱን ሐገር ወደ ትቢያ መከመሪያነት ቀየራት-እንጂ የአረብ ሊጉ መሪ እንዳሉት አማፂያኑን የደማስቆ ቤተ-መንግሥትን ከሚቆጣጠሩበት ደረጃ አላቃረባቸዉም።ደእንዲያዉያም ከተፋላሚ ሐይላት የአሸናፊና ተሸናፊዉን ማንነትን መገመት ከሚያስችልበት ደረጃ ገና አልተደረሰም።

የማራኪሽ ጉባኤተኞች ያሰለፉትን ዉሳኔ በተለይም ለአማፂያኑ ዕዉቅና መሠጠቱን ሩሲያ ተቃዉማዋለች።የሩሲያዉ ዉጪ ጉዳይ ሚንስትር ሰርጌይ ላቭሮቭ እንዳሉት በተለይ ዩናይትድ ስቴትስ ለአማፂያኑ ዕዉቅና የሰጠችዉ ከሰወስት ቀናት በፊት ከሩሲያ ጋር የደረሰችበትን ስምምነት አፍርሳ ነዉ።

«ዕዉቅና መሰጠቱ ጄኔቭ ላይ የተደረሰበትን የጋራ አቋም የሚፃረር ነዉ።የጄኔቩ የጋራ አቋም በሶሪያ መንግሥትና በተቃዋሚዎች ተወካዮች መካካል አጠቃላይ ድርድር እንዲደረግ ነበር።ከሰወስት ቀናት በፊት ጄኔቭ ላይ ባደረግነዉ ምክክር መሠረት የሶሪያ መንግሥትም የሚሳተፍበት አጠቃላይ ድርድር በማድረጉ ጥረት አስፈላጊነት ከአሜሪካዉያን ጋር ተግባብተን ነበር።»

አልሆነም።ዩናይትድ ስቴትስ እንደ አዉሮጳና እንደ መካካለኛዉ ምሥራቅ ሸሪኮዎችዋ ሁሉ የሶሪያ አማፂያን የሶሪያ ብቸኛ ተወካይ ለመሆናቸዉ ዕዉቅና ሰጥጣለች።ጦርነት፥ እልቂት፥ ጥፋቱም ቀጥሏል።ዛሬም ጭምር።

©Christophe Petit Tesson/MAXPPP - 20/08/2012 ; DOMIZ ; IRAQ - Un enfant de refugies kurdes de Syrie au camp de Domiz entre la frontiere syrienne et la ville de Dohuk dans la region autonome du Kurdistan d'Iraq. Pres de 10 000 refugies ont ete accueillis ici depuis le debut des combats en Syrie. A kurd children in Domiz refugee camp, 20 km southeast of Dohuk city, in northern Iraq, on August 20, 2012. UNHCR Camp hosts refugees mainly from the northern Kurd regions of Syria fleeing fighting between the FSA and government forces. *** Local Caption ***
ስደቱምስል picture-alliance/dpa
epa03488718 A handout picture released by the Syrian Arab News Agency (SANA), shows Syrian citizens inspecting the scene of a car bomb attack in Jaramana of Druze majority in Rural Damascus, Syria, 28 November 2012. According to SANA terrorists set off two explosions with two car bombs parked at the main square in the Jaramana neighborhood of rural Damascus. The blast led to a number of death and wounded citizens, and a large amount of damage to surrounding buildings, SANA also stated. EPA/SANA / HANDOUT HANDOUT EDITORIAL USE ONLY/NO SALES +++(c) dpa - Bildfunk+++
ጥፋቱምስል picture-alliance/dpa

ነጋሽ መሐመድ

ሒሩት መለሰ


















ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ