1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የሶርያ መንግሥት ከባለሥልጣናቱ የገጠመው ችግር

ማክሰኞ፣ ነሐሴ 1 2004

የሶርያ ጠቅላይ ሚንስትር ሪዣድ ሂጃብ የፕሬዚደንት በሻር አል አሳድ መንግሥት በራሱ ሕዝብ ላይ ያካሂደዋል ያሉትን የጀምላ ጭፍጨፋ በመቃወም በትናንቱ ዕለት ከድተው የተቃዋሚውን ጎራ መቀላቀላቸው የሚታወስ ነው። የሶርያ መንግሥት ግን ሂጃብ ከሥልጣናቸው እንደተባረሩ ነው ያስታወቀው።

https://p.dw.com/p/15lNZ
Syria's former agriculture minister Riyad Hijab is seen in this file handout photograph distributed by Syrian News Agency (SANA) on June 6, 2012. Syrian Prime Minister Hijab has been sacked, Syrian television reported on August 6, 2012. Syrian President Bashar al-Assad appointed Hijab, a former agriculture minister, as prime minister in June following a parliamentary election in May which authorities said was a step towards political reform but which opponents dismissed as a sham. REUTERS/SANA/Handout (SYRIA - Tags: POLITICS CIVIL UNREST HEADSHOT) FOR EDITORIAL USE ONLY. NOT FOR SALE FOR MARKETING OR ADVERTISING CAMPAIGNS. THIS IMAGE HAS BEEN SUPPLIED BY A THIRD PARTY. IT IS DISTRIBUTED, EXACTLY AS RECEIVED BY REUTERS, AS A SERVICE TO CLIENTS
የሶርያ ጠ/ ሚንስትር ሪዣድ ሂጃብምስል Reuters


የውጭ የፖለቲካ ታዛቢዎች እንደሚሉት፡ የሶርያ ጠቅላይ ሚንስትር እና በሶርያ የተቃዋሚው ወገን ቃል አቀባይ ዘገባ መሠረት፡ ሁለት የመንግሥት ሚንስትሮች እና ሦስት ከፍተኛ የጦር ኃይሉ መኮንኖችም የከዱበት ድርጊት የፕሬዚደንት አሳድ መንግሥት ከውስጥ በገጠመው ተቃውሞ እየፈራረሰ መሆኑን ጠቋሚ ነው። ይህ በዚህ እንዳለ፣ የሶርያ ፕሬዝደንት በሽር አልአሰድ ላለፉት 17 ወራት የተነሳባቸዉ ህዝባዊ ተቃዉሞ ለመጨፍለቅ ቆርጠዉ መነሳታቸዉን አመለከቱ። ከሁለት ሳምንታት ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ በቴሌቪዥን መስኮት ብቅ ያሉት አልአሰድ፤ የሶርያ ህዝብና መንግስት የአሸባሪዎችን ሀገርና ሽብርተኝነትን ለመዋጋት መዘጋጀታቸዉን መግለፃቸዉን ሮይተርስ የሀገሪቱን የዜና ወኪል በመጥቀስ ዘግቧል። አልአሰድ ስለጤና ማጣታቸዉም ሆነ ስለመገደላቸዉ ሲናፈስ የነበረዉን ወሬ ለጉብኝት ደማስቆ ከሚገኙት የኢራን የከፍተኛ ብሄራዊ የደህነት ምክር ቤት ኃላፊ ሳኢድ ጃሊሊ ጋ በመሆን በቴሌቪዥን ብቅ በማለትም መሠረተ ቢስ እንደሆነ አሳይተዋል።

epa03347003 A handout photo made available by the official Syrian Arab News Agency (SANA) shows Syrian President Bashar Assad(R) meeting with Secretary of Iran_s Supreme National Security Council, Saeed Jalili (L), in Damascus, Syria, 07 August 2012. Jalili arrived in Damascus earlier in the day coming from Lebanon on an official visit to discuss the situation of the Iranians abducted outside Damascus, as well as the 17-month-old unrest in Syria. A Syrian rebel group claimed responsibility for holding some 48 hostages - 47 Iranians plus an Afghan. EPA/SANA/HANDOUT HANDOUT EDITORIAL USE ONLY/NO SALES +++(c) dpa - Bildfunk+++
ምስል picture-alliance/dpa

ነቢዩ ሲራክ
አርያም ተክሌ
ሂሩት መለሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ