የቆዳ እና ቆዳ ውጦቶች ኤግዚቢሺን በአዲስ አበባ
ረቡዕ፣ የካቲት 12 2006ከኣፍሪካ ደግሞ 1ኛ። ከዚሁ የተነሳ በከፍተኛ መጠን ወደ ውጪ ከምትልካቸው ምርቶች መካከልም ቆዳና ሌጦ ኣንዱ ሲሆን ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ደግሞ ከጥሬ ቆዳ ይልቅ በከፊል የተቀየሩ ወይንም ወደ ቆዳ ውጤቶች የተለወጡ ሸቀጦችን ወደመላክ እያዘነበለች መምጣቷ ይነገርላታል። በዚህ ሳምንት ደግሞ ኣንድ ዓለም ዓቀፍ የቆዳ ውጤቶች ኤግዚቢሺን በአዲስ አበባ ይካሄዳል። እኛም ይህንኑ ከነገ ጀምሮ እስከ ፊታችን ቅዳሜ ድረስ ለሶስት ቀናት በሚሊኒየም ኣዳራሽ የሚካሄደውን የቆዳ ውጦቶች ኤግዚቢሺን ኣስመልክተን ለዛሬው የኢኮኖሚ ዝግጅታችን ያዘጋጀነውን እንሆ ይዘን ቀርበናል፤ ጤና ይስጥልኝ የተወደዳችሁ የዶቸቬሌ ታዳሚዎች ከዝግጅቱ ጋር ጃፈር ዓሊ ነኝ መልካም ቆይታ።
ለመሆኑ የዚህ የቆዳ ውጤቶች ኤግዚቢሺን ዓላማ ምንድነው? አቶ አብዲሳ አዱኛ የኢትዮጵያ ቆዳ ኢንዱስትሪዎች ማህበር ዋ/ጸሓፊ
አቶ አበበ ተክሉ ደግሞ የቆዳ ኢንዱስትሪዎች ማህበር ሊቀመንበር እና በግሉ ዘርፍም የጥቁር ዓባይ ቆዳ ፋብሪካ ዋ/ስራ ኣስኪያጅ ናቸው።
አቶ ኢስጢፋኖስ ሳሚኤል በዚህ በጀርመን ኣገር የኢትዮጵያ እና የጀርመን የኢኮኖሚ ኮንፍረንሶች ዝግጅት ዋና ኃላፍ ናቸው። ዓላማቸውም የኢትዮጵያን እና የጀርመንን የኢንቨስትመንት እና የንግድ ግንኙነት ማዳበር ሲሆን ነገ በአዲስ አበባ በሚከፈተው እና ኢሊያ ተብሎ በሚታወቀው የቆዳ ውጤቶች ኤግዚቢሺን ላይም የጀርመን ኩባኒያዎች እንሳተፉ መጋበዝ ነው።
ኢትዮጵያ፤ በግብርና ሚ/ር ዓኃዛዊ መረጃዎች መሰረት፤ 60 ሚሊየን ያህል ከብቶች እና 50 ሚሊየን ገደማ በግና ፍየሎች እንዲሁም ከ2,3 ሚሊየን በላይ ግመሎች እንዳሏት ይገመታል። ከዚሁ የተነሳ ኣገሪቱ ቀዳሚ ትኩረት ከምትሰጣቸው ስምንት የኢኮኖሚ ዘርፎች መካከል ኣንዱ ይኸው የቆዳ ዘርፍ ነው። በተያዘው የበጀት ዓመትም፤ የስታስቲክስ መ/ቤት መረጃዎች እንደሚጠቁሙት፤ ከዘርፉ ከግማሽ ቢሊየን ዶላር በላይ የውጪ ምንዛሪ ለመሰብሰብ ታቅዷል።
ጃፈር ዓሊ
ነጋሽ መሓመድ