1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የቡድን ሰባት ውሳኔ እና ሩስያ

ማክሰኞ፣ መጋቢት 16 2006

የቡድን ሰባት ሀገራት መሪዎች ትናንት በዘ ሄግ፣ ኔዘርላንድ ስለዩክሬይን ውዝግብ ለመምከር በጠሩት ልዩ ስብሰባ ላይ፣ ሩስያ የዩክሬይን ግዛት የነበረችውን ክሪሚያን የግዛቷ አካል አድርጋ በመቀበሏ ፣ ሞስኮ

https://p.dw.com/p/1BVac
ምስል Reuters

የፊታችን ሰኔ በሶቺ ልታስተናግደው ታቅዶ የነበረውን የቡድን ስምንት ጉባዔ በብራስልስ ለማካሄድ ወሰኑ። ውሳኔው የተወሰደው ዩክሬይን በክሪሚያ የሚገኘው ጦሯ እንዲወጣ ካዘዘች ከጥቂት ጊዜ በኋላ ነበር። ሩስያን ከቡድን ስምንት ለማግለል የወሰዱትን ውሳኔ ለኑክልየር ጉባዔ በዘ ሄግ የተገኙት የሩስያ ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ሴርጌይ ላቭሮቭ አጣጥለውታል።

ገበያው ንጉሤ

አርያም አብርሀ

ነጋሽ መሀመድ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ