1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የብሪታንያ አንጋፋ ጋዜጣ የስልክ ስለላ እና መዘዙ

ሰኞ፣ ሐምሌ 11 2003

በብሪታንያ አንጋፋዉ- ኒውስ ኦፍ ዘ ወርልድ - የተሰኘዉ ጋዜጣ የግለሰብን ስልክ በመሰለሉ ያስነሳዉ ጥያቄ በአገሪቷ ላይ ከፍተኛ የፖለቲካ ቀዉስ ሳያስነሳ እንደማይቀር እየተነገረ ነዉ።

https://p.dw.com/p/RaUf
ምስል newsoftheworld.co.uk

የብሪታንያዉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዴቪድ ካሜሩን የቀድሞ የብዙሃን ጉዳዮች አማካሪ አንዲ ኮልሰን በብሪታንያ የታዋቂ ሰዎችን ስልክ ንግግር በማዳመጡ የተከሰሰዉ ጋዜጣ - ኒውስ ኦፍ ዘ ወርልድ -ጋር ግንኙነት አላቸዉ ተብለዉ ባለፈዉ እስር መዉረዳቸዉ ይታወሳል። - ኒውስ ኦፍ ዘ ወርልድ -የተሰኝዉ አንጋፋ የብሪታንያ ጋዜጣም ህትመቱን አቁሞአል። በብሪታንያ በተለይም የታዋቂ ሰዎችን እና ንጉሳዊ ቤተሰቦችን የግል ስልክ የማድመጡ ክስ ጠቅላይ ሚኒስትሩንም ሳይጠቀል እንደማይቀር ተገልጾአል። እዚህ እስቱድዮ ከመግባቴ በፊት በለንደን የሚገኘዉን ወኪላችንን ድልነሳ ጌታነህን ስለጉዳዩ ጥይቄዉ ነበር

ድልነሳ ጌታነህን
አዜብ ታደሰ