1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የብሪክስ ጉባኤ ፍፃሜና ተቃውሞው

ረቡዕ፣ መጋቢት 18 2005

5 ቱ የብሪክስ አባላት ብራዚል ሩስያ ህንድ ቻያናና ደቡብ አፍሪቃ ለባንኩ ለታቀደው መነሻ ካፒታል 50 ቢሊዮን ዶላር እኩል ድርሻ እንደሚያዋጡ ተገልጿል ። ይሁንና የብሪክስ ጉባኤን በመቃወም በተጓዳኝ በተካሄደ ሌላ ጉባኤ ደቡብ አፍሪቃ በብሪክስ ቡድን ውስጥ የምትጫወተውን ሚናና የጋራ ባንኩን የማቋቋሙ እቅድ ተተችቷል

https://p.dw.com/p/184vO
ምስል picture-alliance/dpa

ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት በማስመዝገብ ላይ የሚገኙት በእንግሊዘኛው ምህፃር ብሪክስ በመባል የሚጠሩት 5 ሃገራት ደቡብ አፍሪቃ ደርባን ውስጥ ለ2 ቀናት ያካሄዱት ጉባኤ ልዩ ልዩ ውሳኔዎችን በማሳለፍ ዛሬ ተጠናቋል ። የአባል ሃገራቱ መሪዎች በአሁኑ ጉባኤ ከተስማሙባቸው ጉዳዮች አንዱ ምዕራቡ አለም ተፅእኖ የማያደርግበት የጋራ የልማት ባንክ ማቋቋም ነው ። 5 ቱ የብሪክስ አባላት ብራዚል ሩስያ ህንድ ቻያናና ደቡብ አፍሪቃ ለባንኩ ለታቀደው መነሻ ካፒታል 50 ቢሊዮን ዶላር እኩል ድርሻ እንደሚያዋጡ ተገልጿል ።

A man walks past a floral display announcing the 5th BRICS Summit in Durban, March 25, 2013. REUTERS/Rogan Ward (SOUTH AFRICA - Tags: BUSINESS POLITICS)
ምስል Reuters

ይሁንና የብሪክስ ጉባኤን በመቃወም በተጓዳኝ በተካሄደ ሌላ ጉባኤ ደቡብ አፍሪቃ በብሪክስ ቡድን ውስጥ የምትጫወተውን ሚናና የጋራ ባንኩን የማቋቋሙ እቅድ ተተችቷል ።የብሪክስ ጉባኤ ተቃዋሚዎች ከተነጋገሩበት ጉዳይ አንዱ የደቡባዊ አፍሪቃ የልማት ባንክ ያጋጠመው የ40 ሚሊዮን ዩሮ ኪሳራ ነበር ። በባንኩ ሃላፊ በፅሁፍ በወጣው መግለጫ መሰረት ባንኩ በሚያሳዝን ሁኔታ ላይ ይገኛል ። ደቡብ አፍሪቃ አባል የሆነችበት ብሪክስ ሃገሪቱን ይበልጥ ጎዳ እንጂ አልጠቀመም ሲሉ የብሪክስተቃዋሚዎች ይከራከራሉ ። ትናንት ተጀምሮ ዛሬ በተጠናቀቀው የመሪዎች ጉባኤ የብሪክስ መንግሥታት የራሳቸውን ዓለም ዓቀፍ የልማት ባንክ ለማቋቋም ተስማምተዋል ። 2 ቀናት ደርባን ውስጥ በተካሄደው ጉባኤ

Südafrika Luftaufnahme Stadtstrand Durban
ደርባንምስል imago stock&people

የብራዚል የሩስያ የህንድ የቻይናና የደቡብ አፍሪቃ ርዕሳነ ብሄርና መራህያነ መንግሥት ቡድኑ ይበልጥ ከምዕራቡ አለም የኤኮኖሚ ጥገኝነት ለመላቀቅ ፍላጎት እንዳለቸው ገልፀዋል ። የብሪክ አባላት የፋይናንስ ቀውስ መከላከያ ገንዘብ ለማዘጋጀትና ለብሪክስ መንግሥታት የመበደር አቅምን የሚመዝን የራሳቸው የሆነ ድርጅት ለማቋቋም አቅድዋል ። ቻይና በአሁኑ ጊዜ የደቡብ አፍሪቃ ዋነኛ የንግድ አጋር ናት ። ሁለቱ አገሮች በሚያካሂዲት የጋራ የንግድ ልውውጥ የደቡብ አፍሪቃ ድርሻ ዝቅተኛ በመሆኑ መስተካከል እንደሚኖርበት የደቡብ አፍሪቃን የፖለቲካው ሂደት በጥሞና የሚከታተሉት ፓትሪክ ቦንድ አሳስበዋል ። ቦንድ እንደሚሉት በዚህ የንግድ ልውውጥ ደቡብ አፍሪቃ አልተጠቀመችም ።

epa03642252 South African President Jacob Zuma (2-R) with Brazilian President Dilma Rousseff (L), Russian President Vladimir Putin (2-L) and President of the People's Republic of China, Xi Jinping at a breakfast with Captains of Industry at the 5th BRICS summit, Durban, South Africa, 27 March 2013. The 5th BRICS Summit starts today and will see mayor business meetings with delegates from China, Brazil and South Africa. EPA/GCIS/HO
የብሪክስ አባል ሃገራት መሪዎችምስል picture-alliance/dpa

« ከ1990ዎቹ ወዲህ ደቡብ አፍሪቃ የምታካሂዳቸው ንግዶች ፤ የጨርቃ ጨርቅ ፣ የኤሌክትሮኒክስ እቃዎችና የቆዳ አምራች የሃገር ውስጥ ኢንዱስትሪዎችን እድሎች አቃጥለውብናል ። በከፍተኛ የጉልበት ብዝበዛ ፣ በዝቅተኛ ዋጋ ተመርተው በርካሽ በሚገቡ እቃዎች ምክንያት እነዚህ ን በመሳሰሉ ኢንዱስትሪዎች በርካታ የሥራ እድሎችንና ገበያዎችን አጥተናል ። »

የቦንድን ትችት የደቡብ አፍሪቃ የሠራተኞች ማህበር በምህፃሩ COSATU ም ይጋራል ። የኮሳቱ ሃላፊ ስቬሊንዚማ ቫቪ በዚህ ሳምንት መጀመሪያ ላይ SABC በተባለው የደቡብ አፍሪቃ ቴሌቪዥን እንደተናገሩት የብሪክስ አገሮች ለማቋቋም ያሰቡትን ባንክ በጥርጣሬ ነው የሚያዩት ።

ባንክ ከአለም የገንዘብ ድርጅትና ከአለም ባንክ አሠራር በመሰረቱ የተለየ እንዲሆን ግፊት እናደርጋለን ።»

Bildnummer: 59431182 Datum: 24.03.2013 Copyright: imago/Xinhua Police attend a security meeting in Durban, southeastern port city of South Africa, March 24, 2013, ahead of the fifth BRICS summit which will be held on March 26-27 here. (Xinhua/Li Qihua) SOUTH AFRICA-DURBAN-BRICS SUMMIT-SECURITY PUBLICATIONxNOTxINxCHN xns x0x 2013 quer 59431182 Date 24 03 2013 Copyright Imago XINHUA Police attend a Security Meeting in Durban southeastern Port City of South Africa March 24 2013 Ahead of The Fifth BRICS Summit Which will Be Hero ON March 26 27 Here XINHUA left South Africa Durban BRICS Summit Security PUBLICATIONxNOTxINxCHN xns x0x 2013 horizontal
ምስል imago stock&people

« ሂደቱን በጥንቃቄ ነው የምንከታተለው ምክንያቱም ማንኛውም ለወደፊቱ በብሪክስ አገሮች የሚቋቋም ባንክ ከአለም የገንዘብ ድርጅትና ከአለም ባንክ አሠራር በመሰረቱ የተለየ እንዲሆን ግፊት እናደርጋለን ።»

ሃያስያን የጋራው ባንክ ጥሬ እቃዎችን ለማጋበስና ገበያም ለማግኘት ርስበርስ መፎካከራቸው የሚነገርላቸውን አባል ሃገራት በትክክልና ፣ ባልተወሳሰበ ሁኔታ መርዳት መቻሉን ይጠይቃሉ ። በጎርደን የኤኮኖሚ ተቋም የብሪክስ ጉዳዮች አዋቂ አብዱላ ፈራችያ የባንኩ አሠራር ዘመናዊ ከሆነ ይህ አያሳስብም ይላሉ ።

«የብሪክስ የልማት ባንክ በሚቀጥሉት ጥቂት አመታት መሰረታዊ ለውጥ የሚያደርግ ይመስለኛል ። አሠራሩ ዘመናዊ አቅድን ከተከለ በብሪክስ አገሮች ብቻ ሳይሆን በአፍሪቃም ዋና ዋና መሰረተ ልማቶችንና ሌሎችም ፕሮጀክቶችን ለመደገፍ የሚያስችለውን አቅም ያዳብራል ። »

ሉድገር ሻዶምስኪ

ሂሩት መለሰ

ነጋሽ መሐመድ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ